በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጀሪካን ፈሳሽና ደረቅ ሳሙናዎችን እንዲሁም ሌሎች የጽዳት መጠበቂያ ቁሳቁሶችን ሕጋዊ ተጫራቾችን ማጫረት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

የተለያዩ ምግብ ነክ ያልሆኑ ዕቃዎችን ማለትም

  • ጀሪካን ፈሳሽና ደረቅ ሳሙናዎችን እንዲሁም
  • ሌሎች የጽዳት መጠበቂያ ቁሳቁሶችን

ከዚህ በታች ያለውን መስፈርት የሚያሟሉትን ሕጋዊ ተጫራቾችን ማጫረት ይፈልጋል።

ተጫራቾች ማሟሟላት ያለባቸው የጨረታ ግዴታዎች

  • የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚፈልግ 1000 ብር በመክፈል ከቅርንጫፍ ጽ/ቤት መግዛት ይኖርበታል
  • በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው፤ ህገ ተመዝጋቢ የሆነ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር(TIN) ወቀረት ያለው፣እንዲሁም በመንግሰት ግዢ ((Egp ) በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገበ
  • ከዚህ በፈት ጨረታ ተሳትፎ በጥራት አቅረቦት ላበረከተው መልካም የሥራ አፈጻጸም ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል
  • ተጫራቹ የጨረታ ዋጋ 2% (ፐርሰንት) ማስከበሪያ ዋስትና በሲፕዩ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን እና ህጋዊነቱ ለ9ዐ ቀናት መሆን አለበት።
  • የኢንሹራንስና ቼክ ማስያዣ ተቀባይነት የለውም።
  • ተጫራቹ የሚጫረቱበትን ዋጋ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ክልልቅ ጽ/ቤት ነው
  • ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉ 10 (አሰር) ተከታታይ በስራ ቀናትና በስራ ሰዓት ውስጥ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
  • የጨረታው ሰነድ አስተሻሸግ ኦሪጅናል (1) እና ኮፒ (1) በተለያዩ ፖስታ ውስጥ አሽጎ የጨረታ ሰነዱን ማህበሩ ባዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  • በአስረኛው ቀን የጨረታ ሰነድ ማህበሩ ባዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 8፡30 ማስገባት የምትችሉ ሲሆን 8፡35 ሳጥኑ ታሽጎ በእለቱ 8፡40 ተጫራቾቹ ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማህበሩ ግቢ ውስጥ ይከፈታል።
  • ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
  • የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚፈልግ በሥራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ አርብ) ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡00 በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ሲዳማ ክልል ቅ/ጽ/ ቤት በአካል በመገኘት መግዛት ይችላል
  • መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ፡- ከዚህ በታች ባለው ስልክ ቁጥር ዘወትር በሥራ ሰዓት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ

ስልክ፡+046 220 0864

አድራሻ፡ ሀዋሳ ከተማ ሀይቅ ዳር ከፍለ ከተማ ጉዱማሌ ቀበሌ

በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-13
  • Publishing entity: Ethiopian Red Cross Society
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 1000.00 ብር
  • Published: May 02, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders