የኦሮሚያ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ለቢሮ አገልግሎት የሚውል የተለያዩ እቃዎችን ሪሶ ማሽን፣ ኮፒ ማሽን፣ እስካነር እና የመሳሰሉትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 4

የኦሮሚያ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ለቢሮ አገልግሎት የሚውል የተለያዩ እቃዎችን ሪሶ ማሽን፣ ኮፒ ማሽን፣ እስካነር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

  • ሎት 1-ሪሶ ማሽን፣ ኮፒ ማሽን፣ እስካነር፣ ቴሌቭዥን 86"
  • ሎት 2-ፕሪንተር፣ ኮምፒውተር ጥገና በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አቅራቢዎች በጨረታው እንድትሳተፉ ይጋብዛል።

  1. የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የአቅራቢዎች ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
  2. ተጫራቾች በዘርፉ መወዳደር የሚያስችል የታደሰ የንግድ ፍቃድ የግብር ከፋይ መለያ ቲን (TIN) እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (BID BOND) ሎት ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) ሎት 2 ብር 3,000.00 (ሶስት ሺህ ብር) ማቅረብ ይጠበቅበታል።
  4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል ከግዢና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ሶስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 305 መውሰድ ይችላሉ።
  5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 የተከታታይ ቀን በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተገለጸው የመዝጊያ ቀን ቀድመው ሰነዱን ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
  6.  ኤጀንሲው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  7. የጨረታው አሸናፊ ዕቃውን በ5 ቀን ውስጥ ማቅረብ አለበት።
  8. የጨረታ ሰነዱ የሚገኝበት አድራሻ ፡-አዳማ ወንጂ መንገድ የኦሮሚያ አዳሪ ት/ቤት ፊት ለፊት

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር – 022 212 3599/ 09 11-65 97 49/

09 11-06 94 85 መደወል ይቻላል።

የኦሮሚያ ሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጀንሲ


Tender details

  • Deadline: 2026-05-11
  • Publishing entity: Oromia Occupation Competency Assessment and Certification Agency
  • Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
  • Bid document price: 100.00 ብር
  • Published: May 01, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders