የአውሲ ርሱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጨው ማቀነባበርያ ፋብሪካ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ በሐራጅ መሸጥ ይፈልጋል
Description
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
በፍርድ ባለመብት ክብሮም ታረቀኝ ህንጻ ሥራ ተቋራጭ እና የፍርድ ባለዕዳ ሬድ ሲ ጨው ማቀነባበርያ እና ማምረቻ ኃላ/የተ/የግል ማህበር መካከል ስላለው የአፈፃፀም ክርክር የፍርድ ባለዕዳ እንደፍርዱ ሊፈጽም ስላልቻለ በአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አፍዴራ ወረዳ የሚገኝ የፍርድ ባለዕዳ ሬድ ሲ ጨው ማቀነባበርያ እና ማምረቻ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ንብረት የሆነ በ36.000ሜ.ካ ያለ ጅምር የጨው ማቀነባበርያ ፋብሪካ ባለበት ሁኔታ መነሻ ግምቱ ብር 19,581,402.38 (አስራ ዘጠኝ ሚልዮን አምስት መቶ ሰማንያ አንድ ሺህ አራት መቶ ሁለት ከ38/100) የሆነ ንብረት በግልጽ ጨረታ በሐራጅ ይሸጣል።
- ለንብረቱ መሸጥ ምክንያት የሆነውና በፍርድ የተወሰነው የገንዘብ ልክ ብር 8,146,668.558 (ስምንት ሚልዮን አንድ መቶ አርባ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስልሳ ስምንት ከ558/100) ነው።
- ንብረቱን ተጫርተው ለመግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች በሚጫረቱበት ወቅት የንብረቱ ግምት 1/4ተኛ በቼክ ማስያዝ አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊዎች አሸናፊ የሆነበትን ገንዘብ በ5 ቀን ውስጥ አጠቃለው ገቢ ማድረግ አለበት አለባቸው።
- የሀራጁ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከተነገረበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት አየር ላይ ይቆያል።
- የጨረታው አሸናፊ የሆነ አካል በጨረታ ለገዛው ንብረት ዋጋውን ሣይከፍል ወይም ግዴታውን ሣይፈጽም ቀርቶ ንብረቱ በ2ኛ ጨረታ ቢሸጥ ዋጋው የቀነሰ እንደሆነ ልዩነቱንና ኪሣራውን እንዲከፍል ይገደዳል።
የአውሲ ርሱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-06-04
- Publishing entity: የአውሲ ርሱ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
- Bid bond: 25%
- Published: May 06, 2026
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.