ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ. የውስጥ ማስዋብ የማጠናቀቂያ ሥራዎች/ዕቃዎች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት/መግዛት ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ከዚህ በታች በቀረበው መሠረት፣ የውስጥ ማስዋብ የማጠናቀቂያ ሥራዎች/ዕቃዎች፣ በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት/መግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
ዓይነት |
የጨረታ ቁጥር |
የጨረታ ማስከበሪያ (ብር) |
|
1 |
የህንጻው የውስጥ ክፍሎች ዲዛይንና ማስዋብ ሥራዎች (Interior Design Works) |
17/2018 |
150,000 |
|
2 |
የሠራተኞች ካፍቴሪያ ዲዛይንና ግንባታ የውስጥ ማስዋብ ሥራ |
18/2018 |
50,000 |
|
3 |
የጽሕፈት እቃዎች (ቶነር 151ኤ) |
19/2018 |
20,000 |
|
4 |
የሠራተኞች የደምብ ልብስ |
20/2018 |
20,000 |
ተጫራቾች ማሟላት የሚጠበቅባቸው፡-
1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና ብቁ ልምድ ያላቸው።
2. ተጫራቾች ከግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ዘወትር በሥራ ሰዓት ናይል ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ዋናው መ/ቤት (ብሔራዊ ቲአትር አካባቢ) ሀብት ሥራ አመራር መምሪያ (22ኛ ፎቅ) በመምጣት ለእያንዳንዱ ጥቅል የማይመለስ ብር 400.00 በመክፈል ስለ ጨረታው የሚገልፀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ።
3. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ከላይ ለእያንዳንዱ በሠንጠረዡ በተገለፀው መሠረት በባንክ የተረጋገጠ ቼክ (ሲፒኦ) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና ከሚጫረቱበት ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን የመጫረቻ ሰነድ እና ዋጋ በኤንቬሎፕ በማሸግ እስከ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 3፡00 ሰዓት ድረስ የኩባንያው ዋና መ/ቤት 22ኛ ፎቅ ላይ ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው በዕለቱ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጧቱ 3፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኩባንያው ዋና መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
6. ኩባንያው ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፦ ናይስ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ዋና መ/ቤት (ብሔራዊ ቴአትር ጀርባ) ሀብት ሥራ አመራር መምሪያ (22ኛ ፎቅ)
የስልክ ቁጥር፡- 0911 430 292 / 0910 068 772
አዲስ አበባ።
Tender details
- Deadline: 2026-05-30
- Bid closing time: 09:00
- Bid opening: 2026-05-30 09:15
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Nile Insurance Company S.C.
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: 400.00 ብር ለእያንዳንዱ ጥቅል
- Published: May 17, 2026
- Posted at: 2026-05-18T11:58:49.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.