የምስራቅ ጎጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የተለያዩ የመኝታ ጊዜ አልባሳትን መግዛት ይፈልጋል
Description
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የምስራቅ ጎጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ የተለያዩ የመኝታ ጊዜ አልባሳትን መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በዘርፉ ፈቃድ ያላችሁ እና በጨረታዉ መሳተፍ የምትፈልጉ፤ እንዲሁም መስፈርቱን የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ትችላላችሁ።
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው።
- የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 1,000 (አንድ ሽህ ብር) በመክፈል ደብረ ማርቆስ በሚገኘው ምስ/ጎጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት አብማ መስመር ዶ/ር ይልቃል የዓይን ህክምና ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከቢሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) የሚወዳደሩበት የስራውን ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ብቻ ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 7 ተከታታይ የስራ ቀናት ዉስጥ የጨረታ ሰነዱን ሞልተዉ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው በ7ኛው ቀን 9፡00 ላይ ይታሸጋል በዚያዉ ቀን 10፡00 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ሰለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ምስራቅ ጐጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 771 34 05 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።
የምስራቅ ጐጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-05-25
- Bid closing time: 15:00
- Bid closing (note): ጨረታው በ7ኛው ቀን 9፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-05-25 16:00
- Bid opening (note): ጨረታው በ7ኛው ቀን 10፡00 ሰዓት
- Region: Amhara
- Publishing entity: የምሥራቅ ጎጃም ዞን አልማ ልማት ጽ/ቤት
- Bid bond: 1%
- Bid document price: 1,000 ብር
- Published: May 18, 2026
- Posted at: 2026-05-21T09:08:39.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.