Post-harvest and processing equipment

ወንዶ ንግድና ኢንቨስትመንት ኩባንያ ኃ/የተ/የግል ማህበር የቡና መፈልፈያ ማሽን፣ የአሻራ መሳቢያ ሞተር ፖምፕና ልዩ ልዩ መለዋወጫ ግዥ በብሔራዊ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

ወንዶ ንግድና ኢንቨስትመንት ኩባንያ ኃ/የተ/የግል ማህበር

  • የቡና መፈልፈያ ማሽን የአሻራ መሳቢያ ሞተር ፖምፕና ልዩ ልዩ መለዋወጫ ግዥ

 በብሔራዊ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ ሰነድ ቁጥር 007/2018 በብሔራዊ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች በተዘረዘረው መስፈርት መሰረት የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንድትሳተፉ እየገለጽን፡-

  1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈለ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፤
  2. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ በጨረታ ለመሳተፍ የሚችሉ ለመሆናቸው ከሚመለከተው ህጋዊ አካል የተፃፈ የታደሰ የታክስ ክሊራንስ ማስረጃ ምዝገባ ሰርተፍኬት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
  3. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታው ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት በአዲስ አበባ ዋናው መ/ቤት በሚገኘው መስቀል አደባባይ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ፊንፊኔ ህንፃ 7ኛው ፎቅ ወንዶ ንግድና ኢንቨስትመንት ፋይናንስ ግዥ ንብረት አስተዳደር መምሪያ መግዛት ይችላሉ።
  4. ማንኛውም ተጫራች ብር 50,000.00 (ሀምሣ ሺ) የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ /CPO/ ከጨረታው ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርቸዋል፤
  5. አሸናፊው ድርጅት በ5 ቀናት ውስጥ የአሸነፈውን ዕቃ ሙሉ በሙሉ ማቅረብ አለበት።
  6. የጨረታ መዝጊያው ሰዓት ከደረሰ እና የጨረታ ሣጥኑ ከታሸገ በኋላ የሚቀርቡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም፡
  7. ማንኛውም ተጫራች በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችልም።
  8. ጨረታው አ.አ መስቀል አደባባይ ፊንፊኔ ህንፃ ወንዶ ንግድና ኢንቨስትመንት ኩባንያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ፋይ/ግዥ/ንብ/አስ/መምሪያ 7ኛ ፎቅ የሚከፈት ይሆናል።
  9. የጨረታው አሸናፊ እንደታወቀ የውል ማስከበሪያ የአሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 10% በማስያዝ ዕቃውን አሟልቶ ማቅረብ ይገባል።
  10. ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ለመገኘት ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም የሚከፈት ይሆናል።
  11. የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት 16ኛው (አስራ ስድስተኛው) ቀን ላይ ቀኑ የሥራ ቀን ከሆነ በዕለቱ ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡30 ሰዓት በዋናው መ/ቤት አዲስ አበባ ይከፈታል።
  12. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፡- መስቀል አደባባይ እስጢፋኖስ ቤተ-ክርስቲያን ፊት ስፌት ፊንፊኔ ህንፃ 7ኛ ፎቅ

ስልክ ቁጥር 011 552 1009/ 011 552 1458/ ፖ.ሣ.ቁ, 9515 ፋክስ 011 551 3654

ወንዶ ንግድና ኢንቨስትመንት ኩባንያ

ኃ/የተ/የግል ማህበር


Tender details

  • Deadline: 2026-08-13
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid closing (note): የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት 16ኛው (አስራ ስድስተኛው) ቀን ላይ ቀኑ የሥራ ቀን ከሆነ በዕለቱ ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-13 14:30
  • Bid opening (note): የጨረታ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት 16ኛው (አስራ ስድስተኛው) ቀን ላይ ቀኑ የሥራ ቀን ከሆነ በዕለቱ ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Wendo Trade and Investment Company
  • Buyer address: መስቀል አደባባይ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ፊንፊኔ ህንፃ 7ኛ ፎቅ
  • Bid bond: 50,000.00 ብር
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Jul 29, 2026)
  • Posted at: 2026-07-29T09:50:53.000Z
← Back to all tenders