Commercial and offset printing

የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ በ 2019 በጀት ዓመት የህትመት አገልግሎት ግዥዎች ለመፈጸም አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንዲሳተፍ ይጋብዛል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ በ 2019 በጀት ዓመት የህትመት አገልግሎት ከዚህ ከታች በሎት የተዘረዘሩትን ግዥዎች ለመፈጸም አቅራቢ ድርጅቶች በጨረታው እንዲሳተፍ ይጋብዛል ።

  1. ሎት የህትመት አገልግሎት ግዥ

ስለዚህም፤

  • ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈለና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
  • የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የእቃና የአገልግሎት አቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገቡና ለዚህም የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
  • የግብር የመክፈያ ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያረጋግጥ በግብር ሰብሳቢነት ባለስልጣን የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፤
  • በተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፤
  • ተጫራቾች ጨረታውን ዝርዝር የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በድሬዳዋ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ የግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 210 በመቅረብ መግዛት የሚችል፣
  • ተጫራቾች ጨረታ ማስከበሪያ 3000.00 (ሶስት ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል፤
  • • ተጫራቾች በጨረታ ያሸነፏቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት በ10 ቀን ውስጥ ቢሮ ድረስ ገቢ ማድረግ የሚችል፣
  • ተጫራቾች የሚጫረቱትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት በስራ ስዓት ከላይ በተጠቀሰው ቢሮ በመቅረብ የሚወዳደሩበትን ዋጋ በመሙላት የጨረታ ሰነዱን በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 4 ሰዓት ለጨረታው በተዘጋቸው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል፡፡
  • ጨረታው በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ይታሸጋል፡፡ በዛው እለት ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል፡፡ ይህ ቀን ግን የስራ ቀን ካልሆነ በቀጣይ የስራ ቀን ይከፈታል።

ማሳሰቢያ፡

ቢሮው ጨረታውን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፦ በስልክ ቁጥር 0941410102 መደወል ይችላሉ።


Tender details

  • Deadline: 2026-08-08
  • Bid closing time: 12:00
  • Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-08 12:00
  • Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን 4፡30 ሰዓት
  • Region: Dire Dawa
  • Publishing entity: Dire Dawa Adminsitration Public Service & Human Resource Development Office
  • Bid bond: 3000.00 (ሶስት ሺህ ብር)
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published on: Melekite Dire (Jul 29, 2026)
  • Posted at: 2026-08-04T07:49:32.000Z
← Back to all tenders