Equipment and Accessories

የባሌ ሮቤ ፖሊ ቴክኒክ ሥልጠና ኮሌጅ የተለያዩ ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የባሌ ሮቤ ፖሊ ቴከኒክ ሥልጠና ኮሌጅ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል በመሆኑም

  1. አላቂ የትምህርት ዕቃዎችና ቋሚ አላቂ ዕቃዎች
  2. ቋሚ ዕቃዎች
  3. የፅዳት ዕቃዎች
  4. የፅሕፈት ዕቃዎች
  5. ቋሚ አላቂ ዕቃዎች
  6. የሠራተኛ የደንብ ልብስ እና
  7. አላቂ የምርት ዕቃዎች
  8. የመኪና ጎማ (Goma)
  9. የመኪና ጭናት አገልግሎት ማቅረብ የሚችል በቦቲ
  10. Infrastructure ዕቃዎችና Computer, Printer, photocopy, lap Top እና የማሽን ጥገና

 በግልፅ ጨረታአወዳድሮ ከዚህ በላይየተጠቀሱትን ዕቃዎችለመግዛት፤ለማስጠገን፤ መኪና ለመከራየት ስለሚፈልግ የሚከተሉትን የጨረታ መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል።

  1. ዕቃዎችን በጥራት ለማቅረብ የሚያስችል ህጋዊ ንግድ ፍቃድ እና የ2019 ዓ.ም ፍቃዳቸውን ያደሱ
  2. ለጨረታ ማስከበሪያ ጠቅላላ ካቀረቡት ብር 80,000 (ሰማኒያ ሺህ) በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ የሚችል
  3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመከፈል ሰነዱን ከሮቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 3 የዕቃ አቅርቦትና ፋይናንስ አስተዳደር የሥራ ሂደት ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
  4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቮሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  5. ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ገብቶ በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰዓት ለይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  6. አሸናፊዎች ያሸነፉባቸውን ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ በባሌ ሮቤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ንብረት ክፍል ገቢ ማድረግ እና የማስጫኛና የማውረጃ ወጪዎችን ተጫራቾች ይሸፍናሉ።
  7. እቃውን በተጠየቀው እስፔስፊኬሽን ካላቀረበ ኪሳራው የአቅራቢው ድርጅት ነው።
  8. ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  9. ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ መሆን እና QR Code Ricit ማቅረብ ይኖርባቸዋል።

ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች ዕቃዎችን በተባለው ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ማቅረብ እና ሰነድ ከቫት በፊት መሙላት ይኖርበታል።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁ 022 665 1505

የባሌ ሮቤ ፖሊ ቴክኒክ ሥልጠና ኮሌጅ


Tender details

  • Deadline: 2026-08-29
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid closing (note): ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-08-29 10:30
  • Bid opening (note): ጨረታው ማስታወቂያው ከወጣበት በ16ኛው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት
  • Region: Oromia
  • Publishing entity: Bale Robe Poly Technic TVET and College
  • Bid bond: 80,000ብር
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 14, 2026)
  • Posted at: 2026-08-14T08:11:48.000Z
← Back to all tenders