Equipment and Accessories

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 022/18

ድርጅታችን ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

  • በጨረታ አንድ (ሎት 1) እስከ 1,500 ኪግ የመጫን አቅም ያለው በኤሌክትሪክ የሚሰራ የእቃ ማጓጓዣ ጋሪ (Electric Pallet Truck) ብዛት 2 ግዥ
  • በጨረታ ሁለት (ሎት 2) የወረቀት መፍጫ ማሽን (Paper Shredder) ብዛት 1 ግዥ፤
  • በጨረታ ሶስት (ሎት 3) ቁርጥራጭ ወረቀት/ሽፍሻፊ) ማሰሪያ ማሽን (Scrap paper Baler machine) ብዛት 1 ግዥ
  • በጨረታ አራት (ሎት 4) - የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች ግዥ፤

.

አይነት

መለኪያ

ብዛት

1

Mac Computer

በቁጥር

1

2

Desktop Computer

በቁጥር

7

3

Printer

በቁጥር

4

4

Laptop

በቁጥር

9

በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ደፈልጋል። ስለሆነም ጠቅታዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የገንዘብ ሚኒስቴር የዕቃ አቅራቢዎች ምዝገባ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክስ ክሊራንስ ያላቸው ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በድርጅቱ ዋና መ/ቤት (አራት ኪሎ) አዲሱ ህንፃ 1ኛ ፎቅ በሚገኘው የዕለት ገንዘብ ተቀባይ የማይመለስ ብር 300.00 ከፍለው በመግዛት የፋይናንሺያል እና የቴክኒካል የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውን እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማድረግ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነባሩ ህንፃ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በባንከ ክፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባችሁ።

ጨረታው 3/13/18 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ የቴክኒካል መጫረቻ ሰነድ (ከላይ የተገለጸው ለቅደመ ግምገማ የሚያገለግሉ ዶክመንቶች፤ የጨረታ ማስከበሪያ) ብቻ ከሰዓት 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነባሩ ህንፃ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይከፈታል። የፋይናንሽያል የመጫረቻ ሠነዶች የሚከፈቱት ቴክኒካል ተቀባይነት ላገኙት ብቻ ነው። ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።

ስልክ ቁጥር 011-155-5230

ድረ ገፅ (www.ethbspe.org)

አዲስ አበባ

ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት

Berhanena selam printing enterprise


Tender details

  • Deadline: 2026-09-08
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid opening: 2026-09-08 14:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Berhanena Selam Printing Enterprise
  • Buyer address: Addis Ababa, Ethiopia
  • Bid bond: 30,000 (ሰላሳ ሺህ)
  • Bid document price: 300.00 ብር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 16, 2026)
  • Posted at: 2026-08-17T15:08:07.000Z
← Back to all tenders