በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የየካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ኮምፒዩተር እና ጀኔሬተር በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ከአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ መሆን ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 003/2018
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የየካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ዕቃዎች አገልግሎቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ከአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ መሆን ይፈልጋል።
- ሎት 1:- ኮምፒዩተር..................የጨረታ ማስከበሪያ ብር 159600.00
- ሎት 2፡- ጀኔሬተር....................የጨረታ ማስከበሪያ ብር 80000.00
በዚህ መሰረት ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች እና ግለሰቦች በጨረታው እንድትሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢ የሆነና ማስረጃ የሚያቀርብ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ ያላቸው፡፡
- በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ቢሮ ቁጥር 2 ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ አካላት ሲሆኑ ሰነድ ለመውሰድ በሚመጡበት ወቅት ከሚመለከተው አካል ወቅቱን የጠበቀ በጽ/ቤቱ ስም የተፃፈ የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም መወዳደር የሚችሉት በራሳቸው በተመረተ ምርት ብቻ ይሆናል። .
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው ዋጋ ማቅረቢያ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ጨምሮ በመግለፅ ዋናውን እና ኮፒውን በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ ላይ በተጠቀሰው የሥራ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ቁጥር 2 ለዚህ ተብሎ ለተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት እቃ ሳምፕል ጨረታ ከመከፈቱ 3 ቀን በፊት አስቀድሞ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ማንኛውም ሳምፕል የሚያስገባ ተወዳዳሪ በአስራ አንደኛው ቀን ቢያመጣ የማንቀበል መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2፡30-10፡00 ሰዓት ድረስ የካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ፋይናንስ ቢሮ በመገኘት የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታው ከተዘጋ በኋላ የሚመጣ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
- ትምህርት ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ለ10/አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ በ11ኛው ቀን በ3:30 ሰዓት ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች የገዛችሁትን ሙሉ ሰነድ ከዋጋ ማቅረቢያው ጋር አብራችሁ ማስገባት አለባችሁ፡፡ ሙሉ ሰነዱን ያላያያዘ ተጫራች ከውድድር ውጪ ይደረጋል።
- የጨረታው አሸናፊዎች ማሸነፋቸውን ከተረጋገጠበት ቀን ጀምሮ 7/ሰባት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የውል ማስያዣ ባሸነፉባቸው ዕቃዎች ላይ 10% (ፐርሰንት) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝና ተዋውለው እቃዎቹን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የግዥ ውል በሚፈፀምበት ወቅት መ/ቤቱ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተመለከተው የዕቃ ብዛት እስከ 20 በመቶ ሊጨምር ሊቀንስ ይችላል።
- ተጫራቾች በመንግሥት ግዥ ዌብሳይት ላይ ድርጅታችሁ ተመዝግቦ መገኘት አለበት።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011 276 8120 / 011 230 3241 / 011 230 3054 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ፡- አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 አውቶብስ ተራ ወደ መሳለሚያ በሚወስደው መንገድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኮልፌ ቅርንጫፍ አጠገብ የካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ት/ጽ/ቤት የካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-04-25
- Bid closing time: 09:30
- Bid closing (note): ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ለ10/አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ በ11ኛው ቀን በ3:30 ሰዓት
- Bid opening: 2026-04-25 10:00
- Bid opening (note): ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ለ10/አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ቆይቶ በ11ኛው ቀን በ4፡00 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Yekatit 23 General Secondary School
- Buyer address: አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ከአውቶቡስ ተራ ወደ መሳለሚያ በሚወስደው መንገድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኮልፌ ቅርንጫፍ አጠገብ የካቲት 23 አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: 500.00 ብር
- Published: Apr 14, 2026
- Posted at: 2026-04-14T08:09:32.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.