በምስራቅ ጉራጌ ዞን የሶዶ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት የእንስሳት መድኃኒት እና ገረጋንቲ አቅርቦትና ሎደር ማሽን በሰዓት በግልጽ ጨረታ በዘርፉ ፈቃድ ባላቸው አካላቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 08/2018

በምስራቅ ጉራጌ ዞን የሶዶ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ለወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ለእንስሳት ዘርፍ አገልግሎት እና በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ የከተማ ማዘጋጃ ቤቶች የውስጥ ለውስጥ መንገድ አገልግሎት የሚውል

  •  ሎት 1 የእንስሳት መድኃኒት
  •  ሎት2 ገረጋንቲ አቅርቦትና ሎደር ማሽን በሰዓት በግልጽ ጨረታ በዘርፉ ፈቃድ ባላቸው አካላቶች አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

 ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

  1. የዘመኑን ግብር የከፈለ፣ እና ስለመከፈሉ የገቢዎች ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
  2. ቲን ነምበር ያለው እና የቫት ተመዝጋቢ የሆነ
  3. የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ያለው፣
  4. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው፣
  5. ጨረታው የሚቆየው ከ05/08/2018ዓ.ም እስከ 26/08/2018 ዓ.ም ሲሆን ተጫራቾች ዋጋቸውን በፖስታ ፋይናንሻልና ቴክኒካል ለየብቻ በመሙላት ሶ/ወ/ፋ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ቢሮ ቁ/ር 8 በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  6. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በ 26/08/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ታሽጎ በ5፡00 ሰዓት ሶ/ወ/ፋ/ል/ጽ/ቤት የግዢ ኬዝ ቲም ቢሮ ቁ/ር 8 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል።
  7. መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ CPO 15000 /አስራ አምስት ሺህ/ ለእያንዳንዱ ሎት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርበታል።
  9. የጨረታ ማስከበሪያው ለተሸናፊ ድርጅት አሸናፋው ውል መግባቱ ከተረጋገጠ በኋላ ይመለስለታል።
  10. አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱን ከተረጋገጠ እስከ ሶዶ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት በመቅረብ ውል መፈጸም ይኖርበታል።
  11. አሸናፊው ድርጅት ከመስሪያ ቤቱ ጋር ውል ሲፈፅም በግዢ መመሪያ መሰረት የውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይጠበቅበታል።
  12. አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች በፈረሙት ውልመሰረት አሸናፊ የሆኑባቸው መድኃኒቶችና እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ፋይናንስ ጽ/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ ማቅረብ አለባቸው።
  13. ተጫራቾች የመድኃኒትና እቃዎች ዝርዝር የያዘ ሰነድ ሶዶ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 8 በመቅረብ ለእያንዳንዱ ሎት ብር 300 /ሶስት መቶ / በመክፈል ሰነድ መሰድ ይችላል።

ለበለጠ መረጃ፡-046 883 0128

በማ/ ኢ/ ክ/ መ/ ምስራቅ ጉራጌ ዞን የሶዶ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት

ቡኢ


Tender details

  • Deadline: 2026-05-04
  • Bid closing time: 10:30
  • Bid opening: 2026-05-04 11:00
  • Region: Central Ethiopia
  • Publishing entity: Sodo Woreda Finance Office
  • Bid bond: 15,000.00 ብር ለእያንዳንዱ
  • Bid document price: 300.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Published: Apr 13, 2026
  • Posted at: 2026-04-14T12:35:40.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders