የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍ/ቤት የኤሌክትሮኒክስ ግዥ፣ ሞተር ግዥ እና የመኪና ከርቮዬ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ 07/2018

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍ/ቤት ለመ/ቤቱ ሰባቱ ለሥራ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች የተገለጸውን እቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ።

  • ሎት 1 የኤሌክትሮኒክስ ግዥ
  • ሎት 2 ሞተር ግዥ
  • ሎት 3. የመኪና ከርቮዬ

በዚህ መሠረት፡-

  1. በየዘርፉ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያለው፣ የዘመኑን ግብር የገበረ
  2. የቫት /VAT/ ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ያለው
  3.  የግብር ክፋይ /TIN/ መለያ ቁጥር ያለው
  4. የዕቃና የአገልግሎት አቅራቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ ድርጅቶች
  5. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፊ ከተራ ቁጥር 1- 4 የተጠቀሰውን ማስረጃዎች ኦርጅናልና ኮፒ ማቅረብ ይገባዋል።
  6. ተጫራቾች የጨረታውን ሠነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ዉስጥ ሰነዱን ለያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 200 / ሁለት መቶ ብር / ብቻ በሲዳማ ክልል ገቢዎች ባለሥልጣን በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000347602028 በማስገባት አስሊፕ ይዞ ሲዳማ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቢሮ ቁጥር 230 ጋር በመቅረብ ሠነዱን መውሰድ ይቻላል።
  7. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ በCPO/ BID Bond 90 ቀን ብር 15,000 /አስራ አምስት ሽህ / በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስም በማሰራት ማቅረብ የሚችል።
  8. ተጫራቾች የፋይናሻል ዶክመንት ኦርጂናል 1 እና 2 ኮፒ በተለያየ በሰም በታሸገ ኢንቬሎፕ ለጨረታ በተዘጋጁ ሣጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል እንዲሁም ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጂናል 1 እና ኮፒ 1በተለያየ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  9. ጨረታው አየር የሚዉልበት ጊዜ ተከታታይ 10 የስራ ቀናት ሲሆን በ11ኛው ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተዘግቶ 8፡45 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ በዓል / የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተገለጸው ስዓት ይከፈታል።
  10. የጨረታ አሸናፊ ዕቃውን በራሱ ወጪ አጎጉዞ መጋዝን ማስገባትና ሰነዱ ላይ በተገለጸዉ መሰረት አገልግሎቱን ማቅረብ ይኖርበታል።
  11. የጨረታው አሸናፊ በጨረታ መመሪያ መሠረት የጨረታ አሸናፊነቱ ማስታወቂያ ይገለጻል።
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 046 212 5584 ደዉሎ መጠየቅ ይቻላል

የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ጠቅላይ ፍ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-04-30
  • Bid closing time: 14:30
  • Bid closing (note): ጨረታው አየር የሚዉልበት ጊዜ ተከታታይ 10 የስራ ቀናት ሲሆን በ11ኛው ከቀኑ 8፡30 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-04-30 14:45
  • Bid opening (note): ጨረታው አየር የሚዉልበት ጊዜ ተከታታይ 10 የስራ ቀናት ሲሆን በ11ኛው ከቀኑ 8፡45 ሰዓት
  • Region: Sidama
  • Publishing entity: Sidama National Regional State Supreme Court
  • Bid bond: 15,000.00 ብር
  • Bid document price: 200.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Published: Apr 18, 2026
  • Posted at: 2026-04-18T08:16:51.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders