ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ አስቸኳይ የጨረታ ማስታወቂያ

ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ በወሊድ ወቅት ችግር የሚገጥማቸውን እናቶች ከስድሳ-አምስት አመታት በላይ የነፃ ሕክምና እየሰጠ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን፣ ከነፃ ሕክምናው በተጨማሪ በሐምሊን የአዋላጅ ነርሶች ት/ቤት በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ፤ እንዲሁም በቡራዩ ልዩ ዞን በሚገኛው የደስታ መንደር መልሶ ማቋቋም ማዕከል፡ በምንሰጠው ሕክምና ለዳኑና ተጨማሪ የቅርብ ክትትል ለሚያስፈልጋቸው እናቶች የራስ-አገዝ የሙያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።

በዚሁም መሠረት ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ከላይ የተገለፁትን አገልግሎቶች መስጠት እንዲችል፣ ልዩ ልዩ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::

ጨረታው ከሚያዚያ 11፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፣ ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማክሰኞ ሚያዚያ 20፣2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል::

ተወዳዳሪ ድርጅቶች ዝርዝር የጨረታውን መመሪያ፣ እንዲሁም ግዢ የሚፈፀምባቸውን የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች አይነትና ብዛት የሚገልፀውን ሰነድ፡ የማይመለስ ብር 350.00/ሦስት መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ የፋይናንስና ግዢ ክፍል መውሰድ ይችላሉ::

ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ይህንን ጨረታ በከፊል ወይንም በሙሉ ለመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው::

ተወዳዳሪ ድርጅቶች ጨረታውን በተመለከተ ለሚያስፈልጋቸው ማናቸውም  ተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-371-65-44/45/46-የውስጥ መስመር 125/198/199 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ::

ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ

ስልክ ቁጥር 011-371-65-44/45/46


Tender details

  • Deadline: 2026-04-27
  • Bid closing time: 17:00
  • Bid closing (note): ከሚያዚያ 11፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት
  • Bid opening: 2026-04-28 14:30
  • Bid opening (note): ሚያዚያ 20፣2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Hamlin Fistula Ethiopia
  • Buyer address: Kolfe Keranyo Sub city woreda 09, House number 920 Betel Hospital Street behind Augusta Shirt Factory
  • Bid document price: 350.00 ብር
  • Published: Apr 19, 2026
  • Posted at: 2026-04-20T11:28:46.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders