ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Description
ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ አስቸኳይ የጨረታ ማስታወቂያ
ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ በወሊድ ወቅት ችግር የሚገጥማቸውን እናቶች ከስድሳ-አምስት አመታት በላይ የነፃ ሕክምና እየሰጠ የሚገኝ በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን፣ ከነፃ ሕክምናው በተጨማሪ በሐምሊን የአዋላጅ ነርሶች ት/ቤት በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ፤ እንዲሁም በቡራዩ ልዩ ዞን በሚገኛው የደስታ መንደር መልሶ ማቋቋም ማዕከል፡ በምንሰጠው ሕክምና ለዳኑና ተጨማሪ የቅርብ ክትትል ለሚያስፈልጋቸው እናቶች የራስ-አገዝ የሙያ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
በዚሁም መሠረት ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ከላይ የተገለፁትን አገልግሎቶች መስጠት እንዲችል፣ ልዩ ልዩ የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል::
ጨረታው ከሚያዚያ 11፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን፣ ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማክሰኞ ሚያዚያ 20፣2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል::
ተወዳዳሪ ድርጅቶች ዝርዝር የጨረታውን መመሪያ፣ እንዲሁም ግዢ የሚፈፀምባቸውን የሕክምና መገልገያ መሣሪያዎች አይነትና ብዛት የሚገልፀውን ሰነድ፡ የማይመለስ ብር 350.00/ሦስት መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ የፋይናንስና ግዢ ክፍል መውሰድ ይችላሉ::
ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ይህንን ጨረታ በከፊል ወይንም በሙሉ ለመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው::
ተወዳዳሪ ድርጅቶች ጨረታውን በተመለከተ ለሚያስፈልጋቸው ማናቸውም ተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011-371-65-44/45/46-የውስጥ መስመር 125/198/199 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ::
ሐምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ
ስልክ ቁጥር 011-371-65-44/45/46
Tender details
- Deadline: 2026-04-27
- Bid closing time: 17:00
- Bid closing (note): ከሚያዚያ 11፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት
- Bid opening: 2026-04-28 14:30
- Bid opening (note): ሚያዚያ 20፣2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Hamlin Fistula Ethiopia
- Buyer address: Kolfe Keranyo Sub city woreda 09, House number 920 Betel Hospital Street behind Augusta Shirt Factory
- Bid document price: 350.00 ብር
- Published: Apr 19, 2026
- Posted at: 2026-04-20T11:28:46.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.