ኬኛ የግብርና መሣሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ኃላፊነቱ የተ/የግል ማህበር ለድርጅቱ አገልግሎት የሚውሉ የኤሌክትሪክ አዉቶሞቢል እና ሚኒባስ ተሽከርካሪዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 7/2018

ኬኛ የግብርና መሣሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ኃላፊነቱ የተ/የግል ማህበር ለድርጅቱ አገልግሎት የሚውሉ የኤሌክትሪክ አዉቶሞቢል እና ሚኒባስ ተሽከርካሪዎችን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን ማሟላት የሚችሉ ድርጅቶች መወዳደር ይችላሉ።

1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፊኬት በአቅራቢነት ዝርዝር የተመዘገቡ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችልና የመንግስት ግዴታ ስለመወጣቱ የሚያሳይ ክሊራንስ ማቅረብ አለባቸዉ።

2. ይህ ጨረታ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ2፡30-11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከ2፡30-6፡00 ሰዓት ድረስ ከግርጌ በተጠቀሰው አድራሻችን ቀርበው ከድርጅቱ ቢሮ የሀብት አስተዳደር መምሪያ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ።

3. ጨረታዉ በአየር ላይ በዋለ በ11ኛዉ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ ቀን 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል። ሆኖም የጨረታዉ ቀን ዕሁድ ወይም ብሔራዊ በዓል ላይ ከዋለ በሚቀጥለዉ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይሆናል።

4. የጨረታ ፖስታዉን ፋይናንሺያል እና ቅድመ መገምገሚያዎቹን / ቴክኒካል ሰነድ/ በተለያየ ፖስታ ኦሪጂናሉና ኮፒ በመለየት በፖስታ አሽጎ ማቅረብ አለበት።

5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ያስገቡበትን 2% ብር ወይም ከቴክኒካል ሰነድ /ህጋዊ ሰነዶች/ጋር በሰም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።

6. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነዉ።

አድራሻ፡ አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ስልክ ቁጥር 011 614-9253/ 09 11-74-98-96/ 09 32-12-57-60/ ጃፖን ኤምባሲ አካባቢ ራማዳ ሆቴል ፊት ለፊት ስንታየዉ በላይ ህንፃ 6ኛ ፎቅ፤

ኬኛ የግብርና መሣሪያዎች ማምረቻና ጠቅላላ ንግድ ኃላፊነቱ የተ/የግል ማህበር


Tender details

  • Deadline: 2026-05-13
  • Publishing entity: Kegna Agricultural Equipment Manufacturing and General Trading PLC
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 03, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders