ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የተለያዩ ብረታ ብረቶች፣ የኤሌክትሪክ፣ የቧንቧ እና የግንባታ ዕቃዎች ግዥን በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ ጨረታ ቁጥር EAC 032/2018

  1. ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላ.የተ.የግ.ማህበር የተለያዩ ብረታ ብረቶች፣ የኤሌክትሪክ፣ የቧንቧ እና የግንባታ ዕቃዎች ግዥን በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከሚያዚያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡30 – 6፡30 እንዲሁም ከሰዓት በኋላ ከ7፡30 -11፡ዐዐ ድረስ እንዲሁም ቅዳሜ እስከ 6፡30 “ኢትዮ አግሪ ሴፍት ሃላ.የተ.የግ.ማ ጉርድ ሾላ ሴንቸሪ ሞል ፊት ለፊት ወይም ላሜ ዴያሪ ጀርባ ከኤልፎር አግሮ ኢንዱስትሪ አጠገብ በሚገኘው የኢትዮ አግሪ ሴፍት ሕንጻ ላይ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 106 በመቅረብ የማይመለስ ብር 200.00 ብር /ሁለት መቶ ብር/ በመከፈል እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር መለያ ቁጥር ያላቸው፣ የታክስ ከሊራንስ ሰርተፍኬት፣ የአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ እና የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በመያዝ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
  3. ተጫራቾች የሚያቀርቡት
    • አንድ ዋና /Original የጨረታ ሰነድ ለብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ ታሽጐ
    • አንድ ቅጂ /Copy/ የጨረታ ሰነድ ለየብቻው በታሸገ ፖስታ ታሽጐ እንዲሁም፣
    • ሁሉም በአንድ ላይ በትልቅ ፖስታ ውስጥ ተካቶ የታሸገ መሆን አለበት።
    • በዋናውና በቅጂው መካከል ልዩነት ቢፈጠር ዋናው ተቀባይነት ይኖረዋል። ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡ የተሰረዘ ሰነድ በፊርማ መረጋገጥ ይኖርበታል።
  4. ተጫራቾች የተለያዩ ብረታ ብረቶች፣ የኤሌክትሪክ፣ የቧንቧ፣ እና የግንባታ ዕቃዎች ግዥን የሚያቀርቡበትን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የጠቅላላ ዋጋ 2% /ሁለት ከመቶ/ የባንክ ክፍያ ማዘዣ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ባንከ ጋራንቲ ለኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃሊየተ.የግ.ማ በሚል ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  5. የጨረታ ሰነድ ማስገቢያ የመጨረሻ ቀን ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ድረስ ቢሮ ቁጥር 208 ሲሆን፣ ጨረታውን የመክፈቻ ቀን ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾችና ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 106 ተዘግቶ 4፡45 ሰዓት ላይ የሚከፈት ይሆናል።
  6. ከላይ የተገለጸውን መመሪያ ባልተከተሉ ተጫራቾች ላይ ወዲያውኑ ከጨረታው የሚሠረዝ መሆኑን እንገልጻለን።
  7. ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 011 667 6204 ፋክስ ቁጥር 011 673 2006 መጠቀም ይችላሉ/
  8. ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላ.የተ.የሚማ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፈል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ኢትዮ አግሪ ሴፍት ኃላ.የተ.የግ.ማህበር


Tender details

  • Deadline: 2026-05-13
  • Publishing entity: Ethio Agri-CEFT Pvt.Ltd.Co.
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 04, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders