የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት: የቁም ደን ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ

Description

የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት

የቁም ደን ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር OFWE/BA-05/2018

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ

ፊንፊኔ ደንና ዱር እንስሳት ቅ/ጽ/ቤት ስር ሱባ ሰበታ፤ በረክ፤ ጂባት ገዶ፤ በምሥራቅ ሸዋ ድስትሪከት እና እንጦጦ ጫንጮ ድስትሪክቶች የሚያስተዳድሩት የቁም ባህርዛፍ ደን እንዲሁም በምሥራቅ ሸዋ በማህበራት የሚተዳደር ደን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። 

ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ

ፊንፊኔ ደንና ዱር እንስሳት ቅ/ጽ/ቤት ስር ሱባ ሰበታ፤ በረክ፤ ምሥራቅ ሸዋ ድስትሪክት እና እንጦጦ ጫንጮ ድስትሪክቶች የሚያስተዳድሩት የቁም ባህርዛፍ ደን እንዲሁም በምሥራቅ ሸዋ ማህበራት የሚተዳደር ደን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

በመሆኑም፡-

1. የጊንድላ፣ የአጣና፣ የእንጨት መሰንጠቂያ እና ተዛማጅ ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች እና ግለሰቦች እንዲሁም የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ ስለ ጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፅ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ቀበና ሼል /ኦይል ሊቢያ አጠገብ በሚገኘዉ የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 ወይም ጨረታው የወጣበት ፊንፊኔ ደንና ዱር እንስሳት ቅ/ጽ/ቤት በጨረታው መሣተፍ ይችላሉ።

2. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ /የወጣበትን ቀን ጨምሮ/ ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣው ለ15 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።

3. ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ /የወጣበትን ቀን ጨምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት ክፍት ሆኖ ይቆያል።

4. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀንና ሰዓት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለጻል።

5. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።

6. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ፡- WWW.oromiaforest.et  ማግኘት ይችላሉ

በስልክ ቁጥር፡- 011 124 0249 መደወል ይችላሉ

የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-26
  • Bid closing time: 17:00
  • Bid closing (note): የጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
  • Bid opening: 2026-05-26 17:00
  • Bid opening (note): የጨረታው መክፈቻ ቀንና ሰዓት የተለያየ ነው
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Oromia Forest and Wildlife Enterprise
  • Buyer address: አዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ቀበና ኦይል ሊቢያ አጠገብ
  • Bid bond: 5%
  • Bid document price: 200.00 ብር ለእያንዳንዱ
  • Published: May 12, 2026
  • Posted at: 2026-05-12T08:57:51.000Z
  • Buyer website: https://www.oromiaforest.gov.et

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders