በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በማዕ/ጎን/ዞን የማዕ/አ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት ለማዕ/አ/ወ/አስ/ጽ/ቤት G+1 የቢሮ ግንባታ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

በአማራብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በማዕ/ጎን/ዞን የማዕ/አ/ወ/ገንዘብ/ጽ/ቤት ለማዕ/አ/ወ/አስ/ጽ/ቤት G+1 የቢሮ ግንባታ አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማስገንባት ይፈልጋል። ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።

  1. በዘመኑ የታደሰ በስራው የሚመለከተው ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው
  2. የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር TIN/ያላቸው
  3. ለጠቅላላ ስራ ተቋራጭ ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ እና በህንፃ ስራ ተቋራጭ ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ ሆነው በዘመኑ የታደሰ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  4. በተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ እና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-4 የተቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘወ ማቅረብ አለባቸው።
  6. የግንባታ ዝርዝር መግለጫ(ስፔሲፊኬሽን)ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ጨረታ ከወጣበት 06/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 05/10/2018 ዓ/ም 11፡30 ድረስ ለ30 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 35 0/ሶስት መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ከማዕ/አ/ወ/ገንዘብ ጽ/ቤት ገንዘብ ቤት ቢሮ ቁጥር 05 ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና(ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ብር 1.5% በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀዱ ባንኮች በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ(ሲ.ፒ.ኦ)ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ከጽ/ቤቱ ገንዘብ ቤት ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ኮፒ ከፖስታው ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  9. ጨረታው ከ06/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ 05/10/2018 ዓ/ም ድረስ በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በገንዘብ ጽ/ቤት በግ/ንብ/አስ/ሂደት ወይም ቢሮ ቁጥር 04 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ 05/10/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በግዥ ክፍል ቢሮ ቁጥር 04 በ06/10/2018ዓ.ም ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል። ሆኖም የጨረታ መክፈቻው ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም መንግስት በካሌንደር የሚዘጋው ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን እና በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  12. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 04 ድረስ በአካል በመገኘት ማግኘት ይቻላሉ።
  13. ተጫራቾች በጨረታው ካሸነፉ በኋላ ውል በያዙ በ360 ቀናት ውስጥ ሰርተው ማጠናቀቅ የሚችሉ መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል።

ከሚከተሉት ጥፋቶች እና ምክኒያቶች ውስጥ አንዱን የፈፀመ ተጫራች መስሪያ ቤቱ ከጨረታ ውጪ ሊያደርገው ይችላል።

  • በአዋጁ የተቀመጡ ድንጋጌዎችንና የዚህን አዋጅ ለማስፈፀም የወጣውን መመሪያ ሲጥስ ወይም በጨረታ ሰነድ የተመለከቱትን መሰረታዊ ጉዳዮች ሳያሟሉ ሲቀር የተለየ አስተያየትን ለማግኘት ወይም ጨረታውን ለማሸነፍ ለማንኛውም ባለስልጣን ወይም ሰራተኛ መደለያ መስጠቱ ወይም መደለያ የመስጠት ሃሳብ ማቅረቡ በአሳማኝ ሁኔታ ሲረጋገጥ
  • ተወዳዳሪው በጨረታው ሰነድ ላይ የማጭበርበር ተግባር መፈፀሙ ወይም ከሌላ እጩ ተወዳዳሪ ጋር መመሳጠሩ በአሳማኝ ሁኔታ ሲረጋገጥ
  • ተወዳዳሪው የመጫረቻ ሰነዱን በጨረታ ሳጥኑ ካስገባ በኋላ እራሱን ከጨረታ ለማግለል ከፈለገ እና ጨረታው ከመዘጋቱ ቀንና ሰዓት በፊት የማግለያ ሃሳቡን በጨረታ ሳጥኑ ውስጥ ካላስገባ
  • ቀደም ሲል በተሳተፈበት የመንግስት ጨረታ የገባውን ግዴታ ያልፈፀም ከሆነ የጨረታውን ሂደት ለማዛባት የሞከረና የማጭበርበር ድርጊት የፈፀመ እንደሆነ
  • የጨረታ ማስከበሪያ በጥሬ ገንዘብ በመወዳደሪያ ፖስታ ውስጥ አስገብቶ የተገኘ

1/ ለግንባታ ዘርፍ ስራዎች ግዥ አሰሪ መ/ቤቱ በትክክለኛ መረጃ ከተዘጋጀ የመሀንዲስ ዋጋ ግምት በታች የተጋነነ ዝቅተኛ ዋጋ እና ከፍተኛ ዋጋ ሞልተው አሸናፊ ሆነው የሚመረጡ ተቋራጮች ወይም ተጫራቾች ፤

ሀ/ በመንግስት መ/ቤቶች የሚከናወኑ ልዩ ልዩ የግንባታ ፕሮጀክቶች ግዥ ላይ በጨረታ ግምገማ የሚመረጡ አሸናፊዎች የሞሉት ዋጋ ግዥ ፈፃሚ መ/ቤቱ በትከክለኛ ወቅታዊ የገበያ መረጃ በተዘጋጀ የመሃንዲስ የዋጋ ግምት ማለትም የከተማና መሰረተ ልማት ቢሮና ተዋረድ መምሪያዎች በየሩብ ዓመቱ የሚያዘጋጁትን የዋጋ ጥናት በመጠቀም ከዚህ ጥናት ውጪ ሲሆኑ፤ከማዕከላዊ ስታትስቲክስ በማስቀረት የግንባታው አጠቃላይ ስራ/physical progress/100% እንደተጠናቀቀ ከመጨረሻው ዙር ከፍያ ጋር ተደምሮ የሚከፈል ይሆናል።

ለ/ በግንባታ ግዥ ላይ የዋጋ አሞላሉ በአጠቃላይ ሲታይ ለጀኔሬተር፤ የግቢ ውስጥ የአስፋልት ስራ፤ የኤሌክቶሮ መካኒካል ስራዎች እና የመሳሰሉት ላይ ያሉ የነጠላ ዋጋአሞላላቸው ከምህንድስና ግምት አንፃር ሲታይ ከ25% በታች ሆኖ ከተገኘ ከገበያጥናቱ በልጦ በእነዚህ ስራዎች የሚታየውን የገንዘብ መጠን በየደረጃው ከሚፈፀም ክፍያ ቀንሶ በማስቀረት ስራዎች ሲጠናቀቁ ከመጨረሻ ክፍያዎች ጋር ተደምሮ የሚከፈል ይሆናል።

ሐ/ የግንባታ ስራ ክፍያ አፈፃፀምሙ የአሰሪ መ/ቤቱ አማካሪ መሃንዲስ በሚያቀርበው የክፍያ ምስክር ወረቀት መሰረት ሆኖ የተሰራው የግንባታ መጠንና በውሉ መሰረት ሊከፈል ከሚገባው ገንዘብ ጋር ተገናዝቦ /physical and Flnacil Progrs/ ምጥጥን Ratio / አግባብነት እየተረጋገጠ የመጀመሪያ የክፍያ ጥያቂ መቅረብ የሚችለው፤

  • እስክ ብር 100,000,000(አንድ መቶ ሚሊዮን) ለሚያወጣ የግንባታ ግዥ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ ስራ ቢያንስ 5% እና ከዚያ በላይ እንዳጠናቀቀ እና፤
  • ከብር 100,000,000(አንድ መቶ ሚሊዮን) በላይ ለሚያወጣ የግንባታ ፕሮጀክት ደግሞ የፕሮጀክቱ አጠቃላይ ስራ ቢያንስ 2.5% እና ከዚያ በላይ መጠናቀቁ ሲረጋገጥ ክፍያ የሚፈጸም ይሆናል።

መ/ በግዥ አፈፃፀም መመሪያ ቁጥር 1/2003 አንቀፅ 29.2 የግንባታ ዘርፍ ስራዎች የክፍያ የምስክር ወረቀት አፈፃፀም በተመለከተ፡-

  1. በንዑስ አንቀፅ 2 አማካሪ መሀንዲሱ የክፍያ ምስክር ወረቀት ከስራ ተቋራጩ ተዘጋጅቶ በቀረበለት በ7 (ሰባት) ቀናት ውስጥ የጥያቂውን አግባብነት አረጋግጦ ማጠናቀቅ አለበት።ሆኖም አማካሪ መሃንዲስ በ7(ሰባት) ቀናት የጊዜ ገደብ ውስጥ አጠናቆ ባለማቅረቡ በተቋራጩ ላይ ለሚደርሰው የክፍያ መዘግየት ለጉዳት ማካካሻ በክፍያ የምስክር ወረቀቱ እንዲከፈል የታመነበትን የገንዘብ መጠን መሰረት በማድረግ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የማዳበሪያ የወለድ ምጣኔ የሚገኘውን የገንዘብ መጠን ለስራ ተቋራጩ የመክፈል ግዴታ አለበት።
  2. በንኡስ አንቀጽ 3 የክፍያ የምስክር ወረቀት በአማካሪ መሃንዲሱ ተረጋግጦ በቀረበ በ7(ሰባት) ቀናት ውስጥ የመንግስት መ/ቤቱ ተገቢውን ክፍያ ለስራ ተቋራጩ መፈጸም አለበት የሚለው ተሻሽሎ በቀረበ በ15 (በአስራ አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ የመንግስት መ/ቤቱ ተገቢውን ክፍያ ለስራ ተቋራጩ መፈጸም አለበት በሚል ተሻሽሏል።

ውል ሰጪ የመንግስት መ/ቤት ክፍያውን መፈፀም የሚያስችል በጀት እያለው የክፍያ ጥያቂው በቀረበ በ15(የአስራ አምስት) የስራ ቀናት ውስጥ ለስራ ተቋራጩ ክፍያ ባይፈጽም በተቋራጩ ላይ በክፍያ መዘግየት ምክንያት ለደረሰበት ጉዳት ባዘገየበት ቀን ብዛት በክፍያ የምስከር ወረቀቱ የገንዘብ መጠን መሰረት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የማዳበሪያ የወለድ ምጣኔ ለስራ ተቋራጩ ጉዳት ማካካሻ የመክፈል ግዴታ አለበት።

በዚህ መንገድ የተከፈለው የገንዘብ ወጪ በፍታብሄር ህጉ መሰረት በወቅቱ ስራን በአግባቡ ካልመራው የስራ ኃላፊ ወይም ደመወዝ ላይ እየተቀነሰ ለመ/ቤቱ መተካት ይኖርበታል።

ሠ/ የተጨማሪ (Additional) ግንባታዎች እና የለውጥ ስራ (Variation) በተመለከተ በግዥ አፈጻጸም መምሪያ ቁጥር 1/2003 አንቀጽ 19 ተራ ቁጥር 2 ንኡስ ቁጥር 2.3 እና አንቀፅ 29.2 በተራ ቁጥር 4 ላይ የተቀመጡት የአፈጻጸም ስልቶች እስከነመሻሻያዎች በሚመለከተው ተተክተዋል።

  1. በመንገድ ግንባታ፤ በንጹህ መጠጥ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ እና በመስኖ ግድብ ስራዎች ላይ የሚፈጠር የተጨማሪ (Additional) ግንባታዎች እና የለውጥ ስራ (Variation) የቀረበው ጥያቄ ሲታመንት በአንድ የግንባታ ፕሮጀክት ውል ከመጀመሪያ አጠቃላይ ስምምነት ከተደረሰበት የግንባታ ዋጋ የሁለቱ ድምር እስከ 50% ድረስ ብቻ ተፈቅዷል።
  2. በህንፃና በተያያዥ ግንባታዎች ላይ የሚፈጠር የተጨማሪ Additional) ግንባታዎች እና የለውጥ ስራ (Variation) በአንድ የግንባታ ፕሮጀክት ውል ከመጀመሪያ አጠቃላይ ስምምነት ከተደረሰበት የግንባታ ዋጋ የሁለቱ ድምር እስከ 30% ድረስ ብቻ በሚልተተከቷል። ሆኖም ግን ከላይ በተራ ቁጥር 1 እና 2 የተገለጹት የተጨማሪ Additional) ግንባታዎች የሚፈቅዱት የለውጥ ስራ (Variation) አለመኖሩ ከተረጋገጠና የለውጥ ስራ (Variation) ካለ መጠኑ ከተፈቀደው በላይ ካልሆነ ብቻ ይሆናል።
  3. በአንድ የግንባታ ፕሮጀክት ውል መሰረት ከተያዘውና በስምምነት ከተደረሰበት ውጪ የተጨማሪ Additional) ግንባታዎች እና የለውጥ ስራ (Variation) ለሚጠይቅ የገንዘብ እና የጊዜ መጠን ለተጨማሪ እና ለውጥ ስራ እስከ 10% አሰሪ መ/ቤቱ ከአማካሪ መሃንዲስ ጋር በመከባበር በቅድሚያ ውል ተይዞ ክፍያ ሊፈጸም ይችላል።ሆኖም መጠኑ ከ10% በላይ እስከ 30% በሚሆንበት ጊዜ፡-
    • በወረዳ አስተዳደር የሚፈጸሙ የግንባታ ግዥዎች በወረዳ የገንዘብ ጽ/ቤቶች እና የከተማ መሰረተ ልማት ጽ/ቤቶች ፤ የከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በሌላቸው ወረዳዎች የዞኑ የከታማና መሰረተ ልማት መምሪያ በጋራ ይፈጸማል።
    •  በክልል የሚፈጸሙ የግንባታ ግዥዎች በገንዘብ ቢሮ እና በከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ በጋራ በመመካከር ሊታመንበት የሚፈጸም ይሆናል።
  4. በወረዳ አስተዳደር የሚፈጸሙ የግንባታ ግዥዎችን በተመለከተ ከላይ በተራ ቁጥር 3 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከአሰሪ መ/ቤቱ በሚቀርብ ጥያቄ ወይም በራሱ ውሳኔ የክልል ቢሮዎች (ገንዘብ ቢሮ እና ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ) በልዩ ሁኔታ ሂደቱን የመመርመር ስልጣን አላቸው።
  5. ተጨማሪ (Additional) ግንባታዎች እና የለውጥ ስራ (Variation) ፍቃድ ጥያቄ ተፈረፃሚ የሚሆነው የጥያቄው አግባብነት ለመወሰን ስልጣን በተሰጠው አካል ሲታመንበት ብቻ ይሆናል።ይህም ማለት ጥያቄው የከተማና መሰረተ ልማትቢሮና ተዋረድ ተቋሞች ማስረጃ ሲያቀርቡና ተቀባይነት ሲያገኝ ብቻ የሚፈቀድ ይሆናል። ይህን ተግባር ለማከናወን የሚያስችል አደረጃጀት ያላቸው ግዥ ፈፃሚመ/ቤቶች በራሳቸው መሃንዲስ ወይም አማካሪ በመቅጠር ያዘጋጁትን ዲዛይን እና የስራ ዝርዝር በከተማ መሰረተ ልማት ቢሮ ተዋረድ መ/ቤቶች በማጽደቅ ወደ ስራ መግባት ይኖርባቸዋል።
  6. ከአቅም በላይና አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት በሚፈጠር የስራ ለውጥ በአሰሪ የመንግስት መ/ቤቶች ላይ ለሚፈጠረው ተጨማሪ ጊዜና ወጪ ዲዛይን የሚያዘጋጁና የሚያጸድቁ እንዲሁም አማካሪ ባለሙያዎች በክልሉ በስራ ላይ ባሉ ልዩ ልዩ የህግ ማዕቀፎች መሰረት ተጠያቂነት አለባቸው።

ረ/ለግንባታ ዘርፍ ስራዎች ግዥ ለመፈጸም የሚደረግ የሂሳብ ስሌት (አርቲሚቲክ ቼክ) ማስተካከያን በተመለከተ፡-

  1. የሂሳብ ስሌት (አርቲሚቲክ ቼክ)በባለሙያ ወይም የኮሚት አባል የሆነው አማካሪ መሃንዲስ ማስተካከል የሚቻለው ጠቅላላ ዋጋን ብቻ ሲሆን አቅራቢው ከተጠቀመበት እስክርቢቶ በተለየ ቀለም በአንድ መስመር ሰረዝ በማድረግ በአቅራቢው የተሞላውን ጠቅላላ ዋጋ ብቻ በማረም በሂሳብ ስሌት የተገኘውን ትክክለኛ ዋጋ ማስቀመጥ አለበት።
  2. ለፋይናስ ግምገማ ያለፉት ተጫራቾች በቁጥር ፤
    • ቢያንስ 3 (ሶስት) እና በላይ ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ ሒሳብ ስሌት (አርቲሚቲክ ቼክ) ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 2.5% ድረስ ከሆነ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ የበለጠ ልዩነት ካጋጠመ ከውድድር ውጪ ይሆናል።
    • ከ 3 (ሶስት) በታች ከሆኑ በጨረታ አከፋፈት ወቅት ከተነበበው አጠቃላይ ዋጋ ላይ ሒሳብ ስሌት (አርቲሚቲክ ቼክ) ከተሰራ በኋላ የተደረሰበት ልዩነት እስከ 1% ድረስ ብቻ ተቀባይነት የሚኖረው ሲሆን ከዚህ በላይ ከሆነ ከውድድር ውጪ ይሆናል።
  3. የሂሳብ ስሌት (አርቲሚቲክ ቼክ) በግዥ ፈፃሚው መ/ቤት ባለሙያ ከሚስተካከለው ውጪ በተጫራቾች የሚቀርበው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በነጠላ እና ጠቅላላ ዋጋ ላይ ስርዝ ድልዝ ካለ ተጫራቹ ከጨረታ ውጪ ይሆናል።
  4. የግዥ ሰነዶች በሚመለከታቸው ግዥ ባለሙያዎችና ግዥ ፈፃሚ የስራ ክፍል ውስጥ ብቻ በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።
  5. ከላይ የተቀመጡትን መመዘኛዎች ተግባራዊ እንዲሆኑ በቅድሚያ መመዘኛው በተጫራቾቸ መመሪያ ተካቶ ተጫራቾች እንዲያቁት መደረግ አለበት።

ስልክ ቁጥር 09 18 65 33 96/ 09 18 15 46 34

የማዕከላዊ አርማጭሆ  ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-06-13
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid opening: 2026-06-13 10:30
  • Region: Amhara
  • Publishing entity: Central Armacheho Woreda F/E/D/Bureau
  • Bid bond: 1.5%
  • Bid document price: 350.00 ብር
  • Published: May 14, 2026
  • Posted at: 2026-05-14T08:13:08.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders