ለመጽደቅ የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ /Deep Well Drilling Project/ ተቋራጮችን ለማሰራት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ / Deep Well Drilling Project/

ቦታ፦ በደብረ ብርሃን እምዬ ምኒሊክ ክፍለ ከተማ ፣ ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ቀበሌ፣ ቦራሌ ቱሉ አምባ እና ጠንቆሌ የገጠር ንዑስ ቀበሌ።

ለመጽደቅ የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት በደብረ ብርሃን ዙሪያ በሚገኙ 4 የፕሮጀክት ሳይቶች ላይ የ4 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ፣ ግንባታ እና የውሃ ምርታማነት ሙከራ ሥራዎችን ብቃት ባላቸው ተቋራጮች ለማሰራት ይፈልጋል።

  • ለመፅደቅ ሳይት፦ 1 ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ (ከ160-180 ሜትር)።
  • የቦራሌ፣ የጠንቆሌ እና የቱሉ አምባ መንደሮች፦ 3 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች (ከ140-160 ሜትር)።

ተጫራቾች ሊያሟላቸው የሚገቡ መስፈርቶች፦ ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩና የሚከተሉትን ሕጋዊ ማስረጃዎች ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።

  • የዘመኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የዘመኑ የግብር ክሊራንስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ሰነድ።
  • ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ወይም ከሚመለከተው አካል የተሰጠ የደረጃ 5 (WWC/WWD-5) እና ከዚያ በላይ የሆነ የብቃት ማረጋገጫ ምስከር ወረቀት።
  • በመንግሥት የጨረታ እገዳ (Debarment) ውስጥ ያልተካተቱ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ።
  • ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ በሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ይህ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 13 ተከታታይ የሥራ ቀናት (ቅዳሜን ጨምሮ ) ዘወትር በሥራ ሰዓት መተው የማይመለስ 500.00 (አምስት መቶ) የኢትዮጵያ ብር በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
  • ተጫራቾች የቴክኒክ እና የፋይናንስ ሰነዶቻቸውን ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ (አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ) ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ጨረታው በ13ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:00 ሰዓት ታሽጎ፣ በዚያው ቀን በ8:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
  • ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ ፡ አያት ዞን አምስት መንገድ 14 

+251 97 657 2397/ +251 91 361 0673

tojustify24@gmail.com  / info@alemetsdek.com 

አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ለመጽደቅ የዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-27
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ13ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-05-27 14:30
  • Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ13ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:30 ሰዓት
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: ለመጽደቅ ዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published: May 15, 2026
  • Posted at: 2026-05-15T08:56:46.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders