ለመጽደቅ የዘለቄታ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ፣ ግንባታ እና የውሃ ምርታማነት ሙከራ ስራዎችን ብቃት ባላቸው ተቋራጮች ለማሰራት ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
የጥልቅ ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ/ Deep Well Drilling Project/
ቦታ፦ በደብረ ብርሃን እምዬ ምኒሊክ ክፍለከተማ፣ ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ቀበሌ፣ ቦራሌ ቱሉ አምባ እና ጠንቆሌ የገጠር ንዑስ ቀበሌ ለመጽደቅ የዘለቄታ የበጎ አድራጎት ድርጅት በደብረ ብርሃን ዙሪያ በሚገኙ 4 የፕሮጀክት ሳይቶች ላይ የ4 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች ቁፋሮ፣ ግንባታ እና የውሃ ምርታማነት ሙከራ ስራዎችን ብቃት ባላቸው ተቋራጮች ለማሰራት ይፈልጋል።
- ለመፅደቅ ሳይት፦ 1 ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ (ከ160-180 ሜትር)።
- የቦራሌ፣ የጠንቆሌ እና የቱሉ አምባ መንደሮች፦ 3 ጥልቅ የውሃ ጉድጓዶች (ከ140-160 ሜትር)።
ተጫራቾች ሊያሟሏቸው የሚገቡ መስፈርቶች፦ ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩና የሚከተሉትን ህጋዊ ማስረጃዎች ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፦
- የዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፍቃድ፣ የዘመኑ የግብር ክሊራንስ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ምዝገባ ስነድ
- ከውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ወይም ከሚመለከተው አካል የተሰጠ የደረጃ 5 (WWC/WWD-5) እና ከዚያ በላይ የሆነ የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት።
- በመንግስት የጨረታ እገዳ (Debarment) ውስጥ ያልተካተቱ መሆኑን የሚያረጋግጥ ሰነድ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ በሚገኘው የድርጅቱ ቢሮ ይህ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት 11 ተከታታይ የስራ ቀናት (ቅዳሜን ጨምሮ ) ዘወትር በስራ ሰዓት መተው የማይመለስ 500.00 (አምስት መቶ) የኢትዮጵያ ብር በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የቴክኒክ እና የፋይናንስ ሰነዶቻቸውን ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ (አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ኮፒ) ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:00 ሰዓት ታሽጎ፣ በዛው ቀን በ8:30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በድርጅቱ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ፡ አያት ዞን አምስት መንገድ 14
+251 97 657 2397 / +251 91 361 0673 tojustify24@gmail.com / info@lemetsdek.com አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
Tender details
- Deadline: 2026-05-29
- Bid closing time: 14:00
- Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-05-29 14:30
- Bid opening (note): ይህ ማስታወቂያ ከተለቀቀበት ቀን ጀምሮ በ11ኛው ቀን ከሰዓት በኋላ በ8:30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: ለመጽደቅ ዘለቄታ በጎ አድራጎት ድርጅት
- Bid document price: 500.00 (አምስት መቶ ብር)
- Published: May 17, 2026
- Posted at: 2026-05-18T11:00:57.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.