በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ሲስተም ሶፍትዌሮችን እና ሰርቨር ኮምፒዩተሮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል

Description

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የገዥ መለያ ቁጥር ፡ አብክመ/ኢቴቢ/ግ/ጨ/07/2018

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውሉ ሲስተም ሶፍትዌሮችን እና ሰርቨር ኮምፒዩተሮችን ማለትም ፡-

  • ሎት 1- Digital Finance information Management System
  • ሎት 2 Server Computers በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።

ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ህጋዊ ድርጅቶች በጨረታው እንድትሳተፉ ይጋብዛል።

  1. በዘመኑ የታደሰ አግባብነት ያለው የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ።
  2. የግብር ከፋይ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
  3. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
  4. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁ. 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከቴክኒካል ስፔሲፊኬሽን ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
  5. የሚለሙ ሶፍትዌሮችን እና ሰርቨር ኮምፒዩተሮችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ |ቴክኒካል ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማግኘት ይችላሉ።
  6. ተጫራቾች በተቋሙ ዋ/ገንዘብ ያዥ ቢ/ቁ/02 በመምጣትና የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ወይም መግዛት ይችላሉ።
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ የሚወዳደሩበትን የሲስተም ልማትና ሰርቨር ግዥ ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ. ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
  8. ተጫራቾች የቴክኒካል ሰነዳቸውን፣ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት እና ተያያዥ ሰነዶችን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ እንዲሁም የፋይናንሻል (የዋጋ) ሰነዳቸውንና የጨረታ ማስከበሪያቸውን በሌላ ፖስታ በማድረግ ለየብቻ በታሸጉ 2 ፖስታዎች (ቴክኒካልና ፋይናንሻል በማለት) ጨረታው በአዲስ ዘመመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ግዥና ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 20 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  9. ጨረታው በ15ኛው ቀን ከቀኑ በ8፡00 ተዘግቶ በዕለቱ በ8፡30 ጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቢሮ ቁጥር 20 ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ይከፈታል።
  10. አሸናፊው የሚለየው በሎት (ምድብ) ዋጋ ይሆናል።
  11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  12. ተጫራቾች በቴክኒካል ሰነዳቸውና በፋይናንሻል ሰነዳቸው ላይ የድርጅቱን ማህተም ማድረግይጠበቅባቸዋል፡፡ ካላደረጉ ከውድድር ውጪ ይሆናሉ።
  13. በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 20 በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0583206856 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ


Tender details

  • Deadline: 2026-06-22
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid closing (note): ጨረታው በአዲስ ዘመመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰዓት
  • Bid opening: 2026-06-22 14:30
  • Bid opening (note): ጨረታው በአዲስ ዘመመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት
  • Region: Amhara
  • Publishing entity: አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ
  • Bid bond: 1%
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: Jun 08, 2026
  • Posted at: 2026-06-09T08:49:21.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders