ሪዬስ ኢንጂነሪንግ አ.ማ. የተለያዩ የፎርድ መለዋወጫ ዕቃዎች መሸጥ ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
በጨረታ ሰነዱ ላይ ለተዘረዘሩት የተለያዩ የፎርድ መለዋወጫ ዕቃዎች አጠቃላይ መመሪያዎች እና ግዴታዎች፦
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ደንበኞች የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 20 ተከታታይ የስራ ቀናት ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ የሚጫረቱበትን ዋጋ በሰም በታሸገኤንቬሎፕ በማቅረብ በጨረታ ሰነድ ቅጽ ላይ በመሙላትና ለጨረታ ማስከበሪያም ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 10% (አስር በመቶ) በ ሲፒኦ ብቻ በማስያዝ በድርጅቱ የፎርድ መለዋወጫ ዕቃዎች ዲቪዥን ክፍል ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- በዚህ የግዢ ጨረታ የሚቀርቡ ሰነዶች በሙሉ በአማርኛ ወይም በእንግሊዝኛ ቋንቋ መጻፍ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለመግዛት የወሰኑበትን ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስን ሳይጨምር ለእያንዳንዱ መለዋወጫ ዕቃ መለያ ቁጥር በተናጥል መጥቀስ ይኖርባቸዋል። ተጫራቾች የሚፈልጉትን የሚለዋወጫ አይነት በመለየት በጥቅል ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ የፎርድ መለዋወጫ ዕቃዎች ዲቪዥን ገንዘብ ተቀባዮች ቢሮ መግዛት ይችላሉ።
- ከተጠቀሰው ጊዜ በኋላ ዘግይተው የሚቀርቡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
- ጨረታው የጨረታ ሰነዱን ማስገቢያ ጊዜ ከተዘጋበት ቀን ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ የሰራተኞች ክበብ ውስጥ ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊዎች ማሸነፋቸው በማስታወቂያ ከተገለጸ ቀን አንስቶ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ያሸነፉበትን ጠቅላላ ዋጋ የተጨማሪ ዕሴት ታክስን ጨምሮ ክፍያ መፈጸም ይኖርባቸዋል።
- በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ክፍያ ፈጽመው ያሸነፉበትን ዕቃዎች የማያነሱ ከሆነ በእቃዎቹ ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ድርጅቱ ተጠያቂ አይሆንም።
- የጨረታ ተሸናፊዎች ዝርዝር በማስታወቂያ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ለጨረታው ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ. ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር 011 442 1133 / 09 44 06 80 06
ሪዬስ ኢንጂነሪንግ አ.ማ.
Tender details
- Deadline: 2026-08-05
- Publishing entity: Ries Engineering S.C.
- Bid bond: 10%
- Bid document price: 1000.00 ብር
- Published: Jul 14, 2026
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.