የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ቡድን በ2018 በጀት ዓመት ለጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ አስ/ር ቢሮ ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ መሳሪያዎች አወዳድሮ በሎት በጥቅል መግዛት ይፈልጋል
Description
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ቡድን በ2018 በጀት ዓመት ለጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ አስ/ር ቢሮ ግንባታ አገልግሎት የሚውሉ
- ሎት 1. የታቡራታ በር እና
- ሎት 2. የህንፃ መሳሪያ አወዳድሮ በሎት በጥቅል መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች በዘርፉ ንግድ ፈቃድና የቲን ተመዝጋቢ ለመሆናቸዉ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ስለ እቃው የተዘጋጀውን (ስፔስፊኬሽን) በትክክል በማጥናት በዋጋ ማቅረቢያ ሰነዱ ላይ የአንዱንና ጠቅላላ ዋጋ በትክክል መሙላት አለባቸው ሥርዝ ድልዝ ያለበት ዋጋ ማቅረቢያ በተወዳዳሪው ልዩ ፊርማ መረጋገጥ አለበት፡፡
- በዋጋው ማቅረቢያ ላይ የተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል ስም፣ ፊርማና የድርጅቱ አርማ ያለው ማህተም መኖር አለበት፡፡ በተጨማሪ በፖስታው ላይ ያጫራቹን መ/ቤት ስምና የራሳቸው አድራሻ በትክክል ማስቀመጥ አለባቸው፡፡
- በሌላው ዋጋ ተንተርሶ መወዳደር አይፈቀድም፡፡
- የሞሉት ዋጋ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ፖስታ ላይ የንግድ አድራሻውንና ስሙን በመግለጽ በደንብ በታሸገ ፖስታ በማሸግ የሞላዉን ዋጋ ኦርጅናል ፖስታ የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ን/አስ/ቡድን ባዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ከቀረበዉ ጠቅላላ ዋጋ አንድ በመቶ በባንክ የተመሰከረ ሲፒኦ በመሂ 1 ወይም ቢድ ቦንድ በማስያዝ በፖስታዉ ዉስጥ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸል፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ከጨረታዉ ይሰረዛሉ፡፡
- በጨረታው ለተሸነፋ ተወዳዳሪዎች ያስያዙት ገንዘብ የጨረታው አሸናፊ ተለይቶ ውል ከወሰደ በኋላ ይመለስላቸዋል፡፡
- አሸናፊው አሸናፊነቱ ከተገለጸ በኋላ በሚቀጥሉት 5 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉ 5 ተከታታይ ቀናት ዉስጥ የዉል ማስከበሪያ ካሸነፈዉ ከጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ የተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በመሂ 1 በማስያዝ ዉል መያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- በጨረታው ውድድር ወቅት ቅር የተሰኙ ተጫራቾች አሸናፊው በተገለጸ እለት 5 የሥራ ቀናት ቅሬታውን ማቅረብ ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ያለ በቂ ምክንያት ውሉን ካፈረሰ ያስያዘውን ገንዘብ በመቀጫ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡ በህግም እንዲጠየቅ ይደረጋል፡፡
- የጨረታው ሳጥን ከታሸገ በኋላ የሚቀርብ የጨረታ ውድድር ጥያቄ ወይም ማስተካከያ ተቀባይነት የለውም ማስተካከል የሚቻለው ጨረታው ከመከፈቱ ከ2 ቀን አስቀድሞ ማስተካከል ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ አስቀድሞ ከጨረታው መውጣት የሚችሉ ቢሆኑም ያስያዙት ገንዘብ አይመለስም፡፡
- በጨረታ ሰነዱ የተካተቱ ማንኛውም ሰነዶች ገንጥሎ ማስቀረት አይፈቀድም፡፡ ይህንኑ ችላ በማለት ተገንጥሎ የቀረበ የጨረታ ሠነድ ተቀባይነት የለውም፣ ለጨረታው መጓተት በር የሚከፍት በመሆኑ ያስያዘው ገንዘብ አይመለስም፡፡
- የጨረታ ሰነዱ ሙሉ ገጽ መሆኑን ማረጋገጥ ከገዥ ይጠበቃል፡፡
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳችውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ጨረታውን ለማዛባት የሚሞክሩ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ እንደሚሆኑ ለወደፊቱ በመንግስት ግዥ በጨረታ እንዳይሳተፍ እንደሚያደርግና ያስያዙት ገንዘብ እንደሚወረስ ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛውም መስፈርቱን የሚያሟሉ ተጫራቾች ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15 ተከታታይ ቀናት በጋዜጣ ላይ ይቆያል፡፡
- ጨረታው በ16 ተኛው ቀን 4፡00 ይዘጋና በዚሁ ቀን 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ በሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ 20 በመቶ የመጨመርም ሆነ የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- የጨረታ ሠነዱን ቢሮ ቁጥር 06 በመምጣት ብር 400 (አራት መቶ ብር) በመክፈል መዉሰድ ይችላሉ፡፡
- የማስረከቢያ ቦታ ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ንብረት ክፍል ማስረከብ የሚችሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልገዎ በስልክ ቁጥር 058 229 00 50 ደውለው መረጃ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-08-04
- Bid closing time: 10:00
- Bid closing (note): ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16 ተኛው ቀን 4፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-08-04 10:30
- Bid opening (note): ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16 ተኛው ቀን 4፡30 ሰዓት
- Region: Amhara
- Publishing entity: Guagusa Shekudad Woreda FEDB
- Bid bond: 1%
- Bid document price: 400.00 ብር
- Published: Jul 20, 2026
- Posted at: 2026-07-21T10:46:35.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.