Books, manuals and publications
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 02/2019 የ2019 በጀት ዓመት ለተለያየ አገልግሎት ላይ የሚውሉ መጽሔት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል
Description
በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በቁጥር 02/2019 የ2019 በጀት ዓመት ለተለያየ አገልግሎት ላይ የሚውሉ መጽሔት ለማሳተም ከዚህ በታች በተዘረዘረው ዝርዝር መሠረት በሀገር ውስጥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሳተም ይፈልጋል።
- መጽሄት
- አጀንዳ
- ደንብና መመሪያ
- መጽሀፍ
- የደረት ቁጥር
- የተለያዩ መጠን ያላቸው ባነሮች
- MDF ሰርተፊኬት ሲሆኑ
በዚሁ መሠረት፡-
1. በጨረታው ለመወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የቲን እና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
2. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፤
3. ተጫራቾች ጨረታውን በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ጉርድ ሾላ በሚገኘው በፌዴሬሽኑ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውንና ኮፒውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስረኛው ቀን ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት 4፡30 ሰዓት በፌዴሬሽኑ ቢሮ ቁጥር 5 (መሰብሰቢያ አዳራሽ) ይከፈታል።
6. ተጫራቾች ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ እና ሳምፕል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
7. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
ለበለጠ መረጃ፡ 0917012504/0116-47-95-78 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ፋክስ 0116-45-879 - ፖ.ሳ.ቁ 13336
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን
Tender details
- Deadline: 2026-08-20
- Bid closing time: 12:00
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስረኛው ቀን ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት
- Bid opening: 2026-08-20 12:00
- Bid opening (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስረኛው ቀን ከረፋዱ በ4፡30 ሰዓት
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Ethiopian Athletics Federation
- Buyer address: ጉርድ ሾላ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንጻ 2 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6
- Bid bond: 20,000.00 ብር
- Bid document price: 200.00 ብር
- Published on: Reporter (Aug 09, 2026)
- Posted at: 2026-08-10T11:35:18.000Z