House and Building Foreclosure
ጸደይ ባንክ አ.ማ. ስፋቱ 200 ካ/ሜ የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
More tags
Description
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የሀራጅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጸደይ ባንክ አማ ለአቶ ታደሰ አላምረው የሰጠው ብድር ባለመመለሱ ባንኩ በዋስትና መያዣ, የያዘውን በደ/ማርቆስ ከተማ በድሮው ቀበሌ 07 በአሁኑ ቀበሌ 12 በወ/ሮ ጥሩድል ታደስ ስም በካርታ ቁጥር K/07/1006 ተመዝግቦ የሚገኝ ስፋቱ 200 ካ/ሜ የሆነ የመኖሪያ ቤትና ቦታ በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል።
1.ተጫራቾች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ 1/4ኛ በጥሬ ገንዘብ ወይም ሲፒኦ በጸደይ ባንክ ስም ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
2. የቤቱ ጨረታ መነሻ ዋጋው ብር 2,785,000 / ሁለት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰማኒያ አምስት ሺ ብር / ነው።
3. በጨረታ የሚሳተፈው በህግ ሰውነት ያገኘ ድርጅት ከሆነ የድርጅቱን የጸደቀ የመመስረቻ ጽሁፍ እና መተዳደሪያ ደንብ፤ ህጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ህጋዊ ውክልና ማቅረብ አለበት።
4. የጨረታ አሸናፊው አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት በሚመለከተው አካል ጸድቆ በባንኩ ደብዳቤ ሲሰጠው ይሆናል።
5. የጨረታ አሸናፊው ያሸነፈበትን ቀሪውን ገንዘብ በ15 ቀን ውስጥ ለባንኩ በመክፈል ያሸነፈበትን ንብረት መረከብ ይኖርበታል። በዚህ ቀን ውስጥ ካልከፈለ ግን ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው 1/4ኛ ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል።
6. በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ ይመለስላቸዋል።
7. የጨረታ አሸናፊው ከሚገዛው ንብረት ጋር የተያየዙ ማናቸውንም ለመንግስት የሚከፈሉ ክፍያዎች፣ ግብር፣ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ፣ እንዲሁም ከስም ዝውውር ጋር የሚገናኙ ማናቸውም ወጭዎችን ይከፍላሉ። ውዝፍ የሊዝ ክፍያ ካለ ባንኩ የሚከፍል ሲሆን ለቀሪው የሊዝ ክፍያ ገዥው ከሚመለከተው የመንግስት አካል ጋር ይዋዋላል።
8. ተጫራቾች ቤቱን በባንኩ አማካኝነት መጎብኘት ወይም ማየት ይችላሉ።
9. ጨረታው የሚካሄደው ደ/ማርቆስ ከተማ ቀበሌ 12 ለጨረታ በወጣው ንብረት ውስጥ ነው።
10. ጨረታው የሚካሄደው መስከረም 06 ቀን 2019 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ይሆናል።
11. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 21 66 71 15/ 09 12 43 68 68 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
(058 771 2034
* 341
fax 058 771 6667
ቁጠባችን ለነገ ዋስትናችን!
Tender details
- Deadline: 2026-09-16
- Bid closing time: 10:00
- Bid opening: 2026-09-16 10:00
- Region: Amhara
- Publishing entity: Tsedey Bank S.C.
- Buyer address: Legahar Orda Building, 8th Floor room No-804
- Bid bond: 25%
- Published on: Reporter (Aug 12, 2026)
- Posted at: 2026-08-12T09:44:57.000Z