Accounting and Auditing, Accounting System Design

ግሬስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር የ2017/2018 የበጀት ዓመት የሂሳብ እንቅስቃሴውን እና የፋይናስ ሰነዶቹን በሕጋዊ እና በውጪ የተመሰከረለት የኦዲት ድርጅት /External Audit firm/ ለማስመርመር ይፈልጋል

Description

የኦዲት አገልግሎት የጨረታ ማስታወቂያ

የድርጅቱ ስም፡ ግሬስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር

የማስታወቂያ ቀን፡ 08/12/2018

የጨረታ ቁጥር፡ 003

መግቢያ

ግሬስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተወሰነ መሰረታዊ ኅ/ሥ/ማኅበር የ2017/2018 የበጀት ዓመት የሂሳብ እንቅስቃሴውን እና የፋይናስ ሰነዶቹን በሕጋዊ እና በውጪ የተመሰከረለት የኦዲት ድርጅት External Audit firm/ ለማስመርመር ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በዘርፉ የተሰማሩ እና መስፈርቱን የሚያሟሉ የኦዲት ድርጅቶችን በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡

ተወዳዳሪዎች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች

  1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው/ላት፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር TIN Certificate ያለው/ላት፣
  3. የቫት ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችል/ምትችል፣
  4. የሂሳብና ኦዲት ቦርድ AABE የምዝገባ ሰርተፊኬት ያለው/ላት
  5. የዘመኑን ግብር የከፈለ እና ከግብር ሰብሳቢ አካል የታደሰ የግብር ክሊራንስ ማቅረብ የሚችል /ምትችል፣
  6. ተመሳሳይ የስራ ልምድ ያላቸው እና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡

አመላለስ እና የማስገቢያ ጊዜ

  • የሰነድ ማቅረቢያ ቦታ፡ ከአያት አደባባይ ወደ ጎሮ በሚወስደው መንገድ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፊትለፊት ሃላል ሕንጻ 3ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የማኅበሩ ዋና ጽ/ቤት
  • የጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት፡ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቅዳሜን ጨምሮ በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እስከ 13/12/2018 ጠዋት 5፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ይሆናል፡፡
  • ጨረታው የሚከፈትበት ጊዜ፡ በ14/12/2018 ከሰዓት 7፡30 ላይ ተወዳዳሪዎች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማኅበሩ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡

ማሳሰቢያ

  • ኅ/ሥ/ማኅበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  • ለበለጠ መረጃ፡ በ09-72-88-77-77 በስራ ሰዓት ይደውሉ፡፡

መልካም ዕድል

ግሬስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተወሰነ

መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር


Tender details

  • Deadline: 2026-08-21
  • Bid closing time: 11:00
  • Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቅዳሜን ጨምሮ በ5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እስከ 13/12/2018 ጠዋት 5፡00 ሰዓት ድረስ
  • Bid opening: 2026-08-22 13:30
  • Bid opening (note): በ14/12/2018 ከሰዓት 7፡30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: ግሬስ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃ/የተወሰነ መሰረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር
  • Published on: Addis Zemen (Aug 17, 2026)
  • Posted at: 2026-08-18T11:09:05.000Z
← Back to all tenders