Accounting and Auditing, Accounting System Design
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የህ/ሥራ ማህበር ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን የማህበሩን ጠቅላላ ሂሳብ ቅድመ ኦዲት (ሂሳብ ማጣራት) ለማሠራት ይፈልጋል
Description
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/አ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የህ/ሥራ ማህበር ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ያለውን የማህበሩን ጠቅላላ ሂሳብ ቅድመ ኦዲት (ሂሳብ ማጣራት) ለማሠራት ይፈልጋል። ስለዚህ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በማሟላት በጨረታው መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራች ድርጅቶች ቅድመ ኦዲት ሂሳብ ለመስራት የሚያስችል የሙያ ፈቃድ ያላቸው፣
- የዘመኑን ግብር ከፍለው ፈቃዳቸውን ያደሱ፣
- የበጀት ዓመቱን ቅድመ ኦዲት ሂሳብ ለመስራት በሰጠው ዋጋ ላይ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረ ሲፒኦ ሁለት በመቶ ማስያዝ የሚችል፣
- ተጫራቾች የሚያከናውኑትን ተግባር በተመለከተ ከማህበሩ ጋር ዝርዝር ውል ለመፈረም ፈቃደኛ የሆኑ፣
- የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት ምስከር ወረቀት የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ማቅረብ የሚችል፤
- ተጫራቾች ቅድመ ኦዲት የሂሳብ ሥራው የሚከናወንበት የሥራ ዝርዝር እና በመጨረሻ የሚያቀርቡት የሂሳብ ሪፖርት ይዘት እንዲሁም የሚወስድባቸው ጊዜን በተመለከተ የድርጊት መርሐ ግብር የሚያዘጋጁ፣
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ አሥራ አምስት የሥራ ቀናት ጠቅላላ ዋጋቸውን ታክስን ጨምሮ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማህበሩ ጽ/ቤት ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻችን፡-ከሜክሲኮ ወደ ቄራ በሚወስደው መንገድ ሽመልስ ት/ቤት መግቢያ ቂርቆስ ጤና ጣቢያ ምድር ወለል እንገኛለን፡፡
ስልክ ቁጥር፡- 0942-70-57-06, 0911-56-14-62, 0913-54-23-80
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የህ/ሥራ ማህበር
Tender details
- Deadline: 2026-09-09
- Bid closing time: 17:00
- Bid closing (note): ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚታሰብ አሥራ አምስት የሥራ ቀናት
- Bid opening: 2026-09-09 17:00
- Bid opening (note): የጨረታ መክፈቻ ቀንና ሰዓት አልተገለጸም
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የሠራተኞች ገ/ቁ/ብ/ኃ/የተ/የህ/ሥራ ማህበር
- Bid bond: 2%
- Published on: Addis Zemen (Aug 25, 2026)
- Posted at: 2026-08-26T09:27:30.000Z