Accounting and Auditing, Accounting System Design
መሳለሚያ አካባቢ ነጋዴዎች አንድነት አክሲዮን ማህበር የኦዲት/የሂሳብ/ ምርመራ ጨረታ ማስደረግ ይፈልጋል
Description
የኦዲት/የሂሳብ/ ምርመራ ጨረታ
ድርጅታችን መሳለሚያ አካባቢ ነጋዴዎች አንድነት አክሲዮን ማህበር የንግድ ማዕከል ህንፃ ገንብቶ የንግድ ቤቶችን እና ፓርኪንግ በማከራየት የንግድ ስራውን የሚሰራ ድርጅት ነው::
የሂሳብ ምርመራ ዓይነት፡-
1. የ2018 ዓ.ም የገቢ እና የወጪ ሂሳቦችን በዝርዝር እና በተሟላ የኦዲት ምርመራ እንዲከናወንለት ነው:: ይኸውም ፋይናንሻል ሪፖርት ኦዲት እንዳልሆነ እያሳወቅን ምርመራ የሚካሄድባቸው፡-
- የሰነድ እና ዶክመንት ማሟላትና ማረጋገጥ፤
- በገቢ እና ወጪ ሂሳብ ክንዋኔው ያሉት የሂሳብ ጉድለት፣ ጥፋት፣ ስህተቶች፣ ግድፈቶች እና የሕግና መመሪያ መሰራቱን ማረጋገጥ፤
የገቢ እና የወጪ ማከናወኛ ሰነድ መሟላትን ማረጋገጥ፤ - በኦዲቱ ወቅት ከኦዲቱ ጋር በተያያዘ ማንኛውም ፋፈል እና ዶክመንቶች ለሂሳብ ምርመራው ካስፈለገ አስቀርቦ እንዲመረመር ማድረግ፤
- ኦዲቱ ነፃ እና ገለልተኛ ሊሆን ይገባል፤
- የስራ አመራሩ ለኦዲት ስራው ነፃ እና ገለልተኛ ሆኖ ተገቢውን ድጋፍ እና እገዛ ያደርጋል፤
- የመጀመሪያ ድራፍት ሪፖርት ለማኔጅመንት ቀርቦ በኦዲት ባለሙያው አስተያየት ይሰጣል፤
2. የካፒታል ሂሳብ ኦዲት የአ/ማህበሩ አባላት መዋጮ እና ከዚህ ጋር የተያያዙትን ፋይል እና ሰነድ መመርመር የካፒታሎቹን ትክክለኛ መጠን ማረጋገጫ መስጠት
የጨረታ መወዳደሪያ መስፈርት፡-
1. የታደሰ ንግድ ፈቃድ
2. የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት
3. የሙያ ብቃት ማረጋገጫ
4. የስራ ልምድ እና የባለሙያ ፕሮፋል
5. ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ፕሮፖዛል
6. የኦዲት መጠናቀቂያ ጊዜ ለተራ.ቁ 1 ኦዲት እስከ 20 ቀናት ለተራ ቁጥር 2 ኦዲት የሚጠይቀው ጊዜ ታይቶ በሚቀርበው በጋራ የሚወስን
7. በኦዲት የሚቀርበው መወዳደሪያ ዋጋ ለካፒታል ኦዲት እና ለተራ.ቁ 1 የ2018 ኦዲት ለየብቻ ተገልፆ ተጠቅሶ የሚቀርብ ነው፤
8. አ/ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ከወሰደ አይገደድም፤
የማቅረቢያ ጊዜ፡-
- ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ማቅረብ ይቻላል::
ለጽ/ቤታችን የጨረታ ሰነድ በግንባር ለምታቀርቡ
አድራሻ፡- ከአውቶቢስ ተራ አለፍ ብሎ መሳለሚያ ከእሳት አደጋ መቆጣጠሪያ ጽ/ቤት ዝቅ ብሎ አማኑኤል ፀጋ ህንፃ በስተጀርባ ባለው የማህበሩ ህንፃ (ሆናልያት ሞል) 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 402
ማሳሰቢያ
- ማንኛውም መረጃ በስልክ ቁጥር 0911-47-00-14/ 0999-14-88-48 መጠየቅ እና መረዳትይችላሉ::
- በቴሌግራም ለመላክ በ0999-14-88-48
Tender details
- Deadline: 2026-09-10
- Bid closing time: 17:00
- Bid closing (note): ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ማቅረብ ይቻላል
- Bid opening: 2026-09-10 17:00
- Bid opening (note): የጨረታው መክፈቻ ቀን እና ሰዓት አልተገለጸም
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Mesalemia Area Traders Unity S.C.
- Published on: Reporter (Aug 30, 2026)
- Posted at: 2026-08-31T14:45:51.000Z