ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ የተለያዩ አዳዲስ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

ኩባንያችን የካሳ ክፍያ ፈፅሞ የተረከባቸውን እና ከቻይና ሀገር ተገዝተው ጅቡቲ ከደረሱ በኋላ ከጅቡቲ በተሽከርካሪ ተጭነው ወደ አዲስ አበባ በመጓጓዝ ሂደት ላይ ጉዳት የደረሰባቸውን ታርጋ እንዲሁም የባለቤትነት መታወቂያ(ሊብሬ) ያልወጣላቸው የተለያዩ አዳዲስ የኤሌትሪክ ተሽከርካሪዎችን ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።

  • ንብረቶቹን መግዛት የሚፈልጉ ሁሉ በቆርኪ ፋብሪካ ወደ ሚድሮክ ተርሚናል በሚያልፈው አስፋልት መንገድ ገብቶ አሉሙኒየም ፋብሪካ ፊት ለፊት በስተቀኝ በኩል በሚገኘው የኩባንያችን የከባድ ተሽከርካሪዎች ጊዜያዊማቆሚያ ስፍራ ከሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በቦታው በመገኘትእና በማየት የሚገዙበትን ዋጋ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕደንበል ህንፃ 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የኢንጅነሪንግና ሪከቨሪሃንድሊንግ አገልግሎት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ገቢ በማድረግ መጫረት ይችላሉ።
  • ጨረታው ሰኞ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ደንበል ህንፃ 2ኛ ፎቅ በሚገኘው የኢንጅነሪንግና ሪከቨሪ ሃንድሊንግቢሮ ውስጥ ከጧቱ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይከፈታል።
  • ሌሎች ተጫራቾች ባቀረቡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት የተከለከለ ነው።
  • በጨረታ ሰነዱ ላይ የሚቀርበው ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት ሲሆን የጨረታ አሸናፊዎች ያሸነፉበት ዋጋ ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT)15% (አስራ አምስት በመቶ) በተጨማሪነት ይከፍላሉ።
  • ለጨረታ ማስያዣ የሚያቀርቡት ዋጋ የመነሻውን አስር በመቶ (10%) በንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ አ.ማ ስም የተዘጋጀ የባንክ ክፍያ ማዘዣ (CPO) ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
  • በጨረታው ለተካተቱ ንብረቶች ከጨረታው በኋላ ያሉትን ማናቸውም ወጪዎች ገዥው ሙሉ በሙሉ ይሸፍናል።
  • የጨረታ አሸናፊዎች የመክፈያ ቀናቶች ኩባንያው የጨረታ ውጤቱን ካሳወቀበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይአምስት የስራ ቀናት ድረስ ብቻ ሲሆን አሸናፊዎች ክፍያፈፅመው ንብረቶቹን ካልተረከቡ የጨረታው ውጤቱየሚሰረዝ ሆኖ ከላይ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙትገንዘብ ለኩባንያው ገቢ የሚደረግ ሲሆን እንዲሁምየጨረታ አሸናፊዎች ያሸነፉበትን ዋጋ ክፍያ ፈፅመውንብረቶቹን ወዲያውኑ ካልተረከቡ ኩባንያው ሃላፊነቱን የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን።
  • ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማስታወሻ፡-

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09 11 75 35 03፣ 09 11 78 43 39 ይደውሉ

ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ (አ.ማ)


Tender details

  • Deadline: 2026-05-02
  • Bid closing time: 17:00
  • Bid opening: 2026-05-04 10:00
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Nib Insurance Company S.C.
  • Buyer TIN: 0000211714
  • Bid bond: 10%
  • Published: Apr 19, 2026
  • Posted at: 2026-04-20T15:11:03.000Z
  • Buyer website: https://www.nibinsurancethiopia.com/

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders