የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት ጠረጴዛ እና ወንበር ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ካላቸው ተጫራቾች መካከል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል

Description

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ


የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ

  • ጠረጴዛ እና ወንበር

ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ካላቸው ተጫራቾች መካከል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

 ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡

  1. የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ያላቸው፡፡
  3. የግዥው መጠን ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ተመዝጋቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  4. ተጫራቾች የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማረጋገጫ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  5.  አሸናፊው ድርጅት ቅድመ ግብር ተቀናሽ 3 በመቶ ከአሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ ላይ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ዋና እና ቅጂ በማድረግ ከመጫረቻ ሠነዱ ጋር አያይዞ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው፡፡ ጨረታው ሲሞላ ያለምንም ስርዝ ድልዝ መሞላት አለበት፡፡
  7. ጨረታው በጋዜጣ የሚቆይበት ጊዜ ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ21 ቀን ነው፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ሚያዚያ 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ በወጣው ግልጽ ጨረታ ለ21 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡\
  9.  ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን እስከ ግንቦት 02/2018 ዓ/ም ድረስ የማይመለስ ብር 300 (ሦስት መቶ ብር) በመግዛት የጨረታ ሰነዱን ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 ማግኘት ይችላሉ፡፡
  10. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋና እና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ግንቦት 03/2018 ዓም 3፡00 ማስገባት ይችላሉ፡፡
  11. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 በቀን ግንቦት 03/2018 ዓም 3፡00 ታሽጎ 4፡00 ይከፈታል፡፡ የጨረታ መክፈቻ ቀኑ የህዝብ በዓል እና እሁድ ቅዳሜ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  12.  ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 2 በመቶ በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማስያዝ የሚችሉ እና በጥቃቅን የተደራጁ ከሆነ ጥቃቅን ጽ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
  13. የጨረታው አሸናፊ 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ ውል በሚይዝበት ወቅት ማስያዝ ወይም በጥቃቅን የተደራጁ ከሆነ ስራና ስልጠና ጽ/ቤት የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ አለበት፡፡
  14. አሸናፊ ድርጅት የሚሰራቸውን ጠረጴዛ እና ወንበር ስራዎች ማንኛውንም ማቴሪያሎች ወጭ በራሱ አቅርቦ መስራት የሚችል፡፡
  15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበ ነው፡፡
  16. የውድድሩ ሁኔታ በሎት ዋጋ ይሆናል፡፡ በተጨማሪ በአብክመ የግዥ መመሪያ ቁጥር 1/2003 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
  17. የውል ማስከበሪያው ዋስትና ፀንቶ መቆያ ጊዜ ውሉ ከሚጠናቀቅበት የመጨረሻ ቀን በኋላ ቢያንስ ለተጨማሪ 30 ቀናት ፀንቶ መቆየት ይኖርበታል፡፡
  18. አሸናፊ ድርጅት ቅድመ ክፍያ መውሰድ የሚችለው ለሚወስደው ቅድመ ክፍያ ተመጣጣኝ የሆነ መያዣ ወይም ኮላተራል ማስያዝ የሚችል፡፡
  19. ለተጨማሪ መረጃ የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058 224 07 24 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-11
  • Bid closing time: 09:00
  • Bid opening: 2026-05-11 10:00
  • Region: Amhara
  • Publishing entity: የአገው ግምጃ ቤት ከተማ አስተዳዳር ገንዘብ ጽ/ቤት
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 300.00 ብር
  • Published: Apr 20, 2026
  • Posted at: 2026-04-21T11:56:56.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders