በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሻሻመኔ ከተማ መስተዳደር የሻሻመኔ ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ቆጣሪ እና Different Size of Bearings በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ

በኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በሻሻመኔ ከተማ መስተዳደር የሻሻመኔ ከተማ ዉሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት የውሃ ቆጣሪ and Different size of Bearings በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ የሚከተለውን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋበዛል።

1. ዕቃዎቹን በጥራት ለማቅረብ የሚያስችል ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉና የንግድ ፍቃዳቸውን ያደሱ መሆን አለባቸው።

2. ተጫራቾች ለሚያቀርቡት የጨረታ ዋጋ ማስከበሪያ 1% ሲፒኦ ወይም ቢድቦንድ ከሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ጋር ማስያዝ አለባቸው።

3. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በመክፈል ከሻሻመኔ ከተማ ዉሃ አገልግሎት ድርጅት ቢሮ አስተዳደርና ሎጀስቲክ ክፍል በስራ ሰዓት መግዛት ይችላሉ።

4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውን እና ኮፒውን (ቴክኒክና ፋይናንሽል ለየብቻ) በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ (ፖስታ) ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

5. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ በ16ኛው ቀን 6፡00 ሰዓት ተዘግቶ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ በዓል ወይም ዝግ ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ጨረታው ይከፈታል።

6. ተጫራቾች የሚያቀርቡበት ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ጋር መሆኑን ወይም አለመሆኑን መግለጽ ይኖርባቸዋል።

7. ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ተመላሽ የሚሆነው አሸናፊው ድርጅት በፁሁፍ ከተገለፀ በኋላ ይሆናል።

8. የጨረታው አሸናፊ በተጫራቾች መመሪያ በተሰጠው መሰረት የጨረታ አሸናፊነቱ በጽሁፍ እንደተገለጸ አስፈላጊውን የጨረታ ውል ማስከበሪያ ገንዘብ በማስያዝ በሻሸመኔ ከተማ ውኃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ውል መፈራረም አለበት። ይህ ባይፈፀም የጨረታ አሸናፊነቱን በመሰረዝ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለድርጅቱ ገቢ ይሆናል።

9. የእቃዎች ርክብክብ የሚካሄደው በሻሻመኔ ከተማ ውኃ እና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ግምጃ ቤት ይሆናል።

10. የእቃው ብዛት(Quantity) የሚወሰነው በመስሪያ ቤቱ (በድርጅቱ) የበጀት ሁኔታ ላይ ተመርክዞ ነው።

11. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጮች ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ሆኖ ከበጀታችን በላይ የሚሆነውን መቀነስ ወይም መጨመር የምንችል መሆኑን እንገልጻለን።

አድራሻ - የሻሻመኔ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት

ስልክ 09 16 87 16 24 / 09 16 58 16 38 / 09 16 00 24 32 /

የሻሻመኔ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-14
  • Publishing entity: Shashemene Town Water Service Enterprise
  • Bid bond: 1%
  • Bid document price: 500.00 ብር
  • Published: Apr 26, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders