በሠላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ት/ቤት ንብረትነታቸው የማሰልጠኛ ት/ቤቱ የሆኑ የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታና ቦታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
ያገለገሉ ልዩ ልዩ ንብረቶች ሽያጭ ግልጽ ጨረታ የጨረታ ቁጥር CON/TRS/AN./PRO 04/2018
በሠላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ት/ቤት ንብረትነታቸው የማሰልጠኛ ት/ቤቱ የሆኑ የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎችን ባሉበት ሁኔታና ቦታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፤
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ።
- በጨረታው የሚወዳዳሩ ተጫራቾች የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ሰነድ ለመግዛት ሲመጡ ይሄንኑ የሚያረጋገጥ ሰነድ ወይም መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የሆነ ግለሰብም ሆነ ድርጅት በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- በአዲስ አበበና አካባቢዋ የሚገኙ ተጫራቾች በአዲስ አበባ በጃን ሜዳ በሚገኘው የሰላም ማስከበር ማዕከል ግዥ ቢሮና አንዲሁም ድሬዳዋና አካባቢው የሚገኙ ተጫራቾች በሁርሶ የሚገኘው በሰላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ት/ቤት ግዥ ቢሮ ቁጥር 26 በመምጣት የንብረቶችን ዝርዝር መረጃ የያዘ የተጫራቾች መመሪያን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት 200.00 (ሁለት መቶ ብር ) ከፍለው መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች ሰነድ ገዝተው ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 አስከ 11፡00 ሰዓት ልዩልዩ ንብረቶችን ሁርሶ በሚገኘው በሰላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ት/ቤት በመገኘት በአካል መመልከት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚገዙትን ንብረቶች የጨረታውን መነሻ ዋጋ ተሰልቶ ማስያዝ አለባቸው። ለሎት አንድ 40,000.00 (አርባ ሺህ ብር) ለሎት ሁለት 32,000.00 (ሰላሳ ሁለት ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ በማሰልጠኛ ት/ቤቱ ስም በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ በታሸገ ኤንቨኰፕ በማድረግ በሰላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰጠኛ ት/ቤት ጨረታው በሚከፈትበት ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ቀኑ 8፡15 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሳጥኑ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10ኛ ቀን ማለትም ሚያዝያ 29/2018 ከቀኑ 8፡15 ታሽጎ በዚያኑ ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሁርሶ በሚገኘው በሰላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰጠኛ ት/ቤት ትንሿ አዳራሽ ይከፈታል። እንዲሁም ተጫራቹ በራሱ ፍቃድ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስተጓጉለውም።
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለጸላቸው ከሰባት የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ መክፈቴ ይኖርባቸዋል። ሆኖም ሙሉ ከፍያውን በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል።
- የጨረታው መገምገሚያ መስፈርት ዋጋና የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ሲፒኦ) እንዲሁም በጨረታ ሰነዱ የተገለፁትን አሟልቶ መገኘት ነው፡፡ በሰነዱ የተቀመጡትን ሌሎች ነጥቦችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል።
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፋባቸውን ንብረቶች ሙሉ ክፍያ ከፍኰ እስከሚወስድ ድረስ ከውል አተገባበር ዋስትና የሚሆን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ (10%) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለበት።
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በመከፈል ንብረቶቹን በ10 ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ አለባቸው።
- ማሰልጠኛ ት/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 025-447-0115 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
በሰላም ማስከበር ማዕከል የኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ት/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-05-07
- Publishing entity: Ministry of Defense
- Bid bond: በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid document price: 200.00 ብር
- Published: Apr 28, 2026
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.