የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ተሽከርካሪ መሸጥ ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
በአፈ /ከሣሽ ጥሪት ጣውየ ጠባቃ ደሳለኝ መኮነን እና በከፈተከሣሽ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር መካከል ሥላለው የገንዘብ አፈፃጸም ክስ ክርክር ጉዳይ በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ስም ተመዝግቦ የሚገኘው የሰሌዳ ቁጥር ኢት 04-12776 የሻንሲ ቁጥር CWB 450 PHL-07035 የሞተር ቁጥር PF 6-125543 T የሆነ ተሽከርካሪ የአዳስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪ እና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለስልጣን መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ገምቶ በላከው መነሻ ዋ 1,327,029.41 / አንድ ሚሊዮን ሦስት መቶ ሀያ ሰባት ሺህ ሀያ ዘጠኝ ብር ከአርባ አንድ ሳንቲም/ መነሻ ዋጋ በጨረታ እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ ትእዛዝ ሰጥቷል።
በመሆኑም ጨረታ ማስታወቂያው ከሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ ግንቦት 10 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ለ15 ቀን አየር ላይ ቆይቶ ጨረታው ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ ም ከጠዋቱ 3:30 ሰዓት እስከ 6፡30 ሰዓት መኪናው የሚገኘው ወልድያ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመገኘት መጫረት የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን በጨረታ መሳተፍ ወይም መግዛት የሚፈልግ የጨረታ አሸናፊው የአሸነፈበትን 25% /ሃያ አምስት በመቶ/ ለፍርድ ቤቱ ሃራጅ ባይ ባለሙያ ወዲያውኑ እንዲያስይዙ በአስራ አምስት ቀን ውስጥ ሙሉ ገንዘቡን የመክፈል ግዴታ እንዳለበት ዋጋው በጊዜው ካልተከፈለ የስነ ሥርዓት ህጉ በሚያስቀምጠው አግባብ ተጠያቂ ሊሆን እንደሚችል ፍ/ቤቱ አዟል።
የሰሜን ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-05-19
- Publishing entity: North Wollo Zone High Court
- Published: May 02, 2026
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.