ከፍታ የወጣቶች ኃ/የተ/መሰረታዊ የገ/ቁ/ብ/ኅብረት ሥራ ማህበር ኦዲቱ መነሻው (OPENING) 2015 እስከ 2017 ዓ.ም ያለውን የ2017ዓ.ም (IFRS CONVERSION) ሪፖርት ሂሳብ ኦዲት በተፈቀደለት የኦዲት ተቋም አወዳድሮ ማስመርመር ይፈልጋል

Description

IFRS ትግበራ የኦዲት ጨረታ ማስታወቂያ

ከፍታ የወጣቶች ኃ/የተ/መሰረታዊ የገ/ቁ/ብ/ኅብረት ሥራ ማህበር ኦዲቱ መነሻው (OPENING) 2015 እስከ 2017 ዓ.ም ያለውን የ2017ዓ.ም (IFRS CONVERSION) ሪፖርት ሂሳብ ኦዲት በተፈቀደለት የኦዲት ተቋም አወዳድሮ ማስመርመር ይፈልጋል።

ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለጹትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ ትችላላችሁ።

1. የኢትዮጵያ የሂሳብ አያያዝና ኦዲት ቦርድ ወይም እሱ ከሚወከለው አካል ሂሳብ ለመመርመር የሚያስችለውን የሙያ ፈቃድ ያገኘና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፤

2. የዘመኑን ግብር የከፈለ፤

3. በሀገሪቱ ህግ መሰረት የኦዲት ስራ ለመስራት የሚያስችል ወቅታዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለው፤

4. የኅብረት ሥራ ማኅበሩን ሂሳብ ለመመርመር ብቁ ባለሙያዎችን በስራ ላይ ማሰማራት የሚችል ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሚከተለው ማንኛውም ኪሳራና ችግር አስቀድሞ ኃላፊነቱን የሚወስድ፤

5. እንደአስፈላጊነቱ አግባብ ባለው ባለስልጣን የሚጠየቁ ሌሎች መረጃዎችን ማቅረብ የሚችል መሆን አለበት፤

6. የሚወዳደሩበትን የቴክኒካልና የፋይናሻል ፕሮፖዛል በተለያየ ፖስት በማሸግ ማስገባት የሚችል፣

7. ለዚሁ ስራ የተዘጋጀውየስራ መመሪያ (TOR)በመውሰድ፣

8. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ እና ሰነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለ10 የስራ ቀናት ከጠዋቱ 2:30-6፡00 እና ከሰዓት ከ7፡30-10፡30 ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል::

9. ጨረታው ምዝገባው በተጠናቀቀ በቀጣይ የሥራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል:: ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በራሳቸው ምክንያት መገኘት ካልቻሉ ጨረታው በተገኘው ሰው በጨረታ ከኮሚቴ ጋር ይከፈታል::

አድራሻ፡ መገናኛ ዘፍመሽ ፊት ለፊት ታሜጋስ ህንጻ 3ኛ ፎቅ ከፍታ የወጣቶች ኃ/የተ/መሰረታዊ የገ/ቁ/ብ/ኅብረት ሥራ ማህበር ጽ/ቤት

ስልክ: 0116-67-42-66 / 0900 617 020


Tender details

  • Deadline: 2026-05-15
  • Publishing entity: Kefeta Youth Primary SACCO Ltd. Liab
  • Published: May 03, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders