የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፈርኒቸር እና ኤሌክትሪክ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር EEP/TBP/NCB/09/2018

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘሩትን የአቅርቦት ግዥ በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ።

  • ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ በግዥና ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን የአቅራቢዎች ዝርዝር ድረ-ገጽ ላይ የተመዘገቡ መሆን አለባቸው።
  • ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀንና ሰዓት የካ ክ/ከ ወረዳ 9 ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ ፊት ለፊት በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት፣ ትራንስሚሽን ቢዝነስ ግዥ ቢሮ የማይመለስ ብር 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
  •  ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለጹትን ዕቃዎች በሚመለከት የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ዝርዝር በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ቁጥር EEP/TBP/NCB/09/2018 ብሎ በመጻፍ በጨረታ ሰነዱ በተገለጸው መሠረት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  • ተጫራቾች ከዚህ በታች በተዘረዘረው የአቅርቦት ግዥ መወዳደር ይችላሉ።

የአቅርቦት ግዥ ዓይነት

የጨረታ ማስከበሪያ

የጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት

የጨረታው መክፈቻ ቀንና ሰዓት

ሎት1. ፈርኒቸር

ሎት 1. ብር 100,000.00

ግንቦት 18 ቀን 2018 . ከቀኑ 800 ሰዓት

ግንቦት 18 ቀን 2018 . ከቀኑ 830 ሰዓት

ሎት-2. ኤሌክትሪክ እቃዎች

ሎት 2. ብር 100,000.00

  •  ገዥው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  • ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0116732190 መደወል ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል


Tender details

  • Deadline: 2026-05-26
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid opening: 2026-05-26 14:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopian Electric Power
  • Bid bond: 100,000.00 ብር ለእያንዳንዱ ሎት
  • Bid document price: 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/
  • Published: May 11, 2026
  • Posted at: 2026-05-12T07:40:20.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders