በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ንብረትነታቸው የቅ/ጽ/ቤቱ የሆኑ ያገለገሉ የተሽከርካሪ መለዋወጫዎች፣ ጎማዎች ባሉበት ሁኔታና በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል

Description

ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

ያገለገሉ የተሸከርካሪ መለዋወጫዎች እና ተሸከርካሪ ጎማ

ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ECC‐JBO/02/2018

በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ንብረትነታቸው የቅ/ጽ/ቤቱ የሆኑ

  • ያገለገሉ የተሸከርካሪ መለዋወጫዎች ጎማዎች ባሉበት ሁኔታና በግልጽ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በማሟላት ቀርበው በጨረታዉ መወዳደር ይችላሉ።

  1. በጨረታው የሚወዳደሩት ተጫራቾች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሆኖ ሠነድ ለመግዛት ሲመጡ ይህንኑ የሚያረጋግጥ መታወቂያ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
  2. የንብረቶችን ዝርዝር መረጃ፣ የተጫራቾች መመሪያ እና የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በመምጣት የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር ከፍለው መውሰድ ይችላሉ።
  3. ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3፡00 እስከ 5፡30 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ የጨረታ ሰነድ ገዝተው ዕቃዎችን በጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት ተገኝተዉ መመልከት ይችላሉ።
  4. ተጫራቾች በሚገዙት ዕቃዎች የጨረታ የመሸጫ መነሻ ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ (10%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ በታሸገ ኤንቨሎፕ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በሚዘጋበት ቀን እስከ 4፡00 ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  5. የጨረታው መገምገሚያ መስፈርት ጠቅላላ የሎት ዋጋ እና የተሟላ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና እንዲሁም በሰነዱ የተገለጹትን መስፈርቶች አሟልቶ መገኘት ነው።
  6. የሎት የመሸጫ የመነሻ ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ (10%) ያላስያዘ እና በሠነዱ የተቀመጡ ሌሎች መስፈርቶችን ያላሟላ ተጫራች ከጨረታው ውድቅ ይደረጋል።
  7.  የሚዘጋጀው የጨረታ ማስከበሪያ ወይም ሲ.ፒ.ኢ.ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ብቻ የተዘጋጀ መሆን ይኖርበታል።
  8.  ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ሆኖም የመክፈቻ ቀኑ እሁድ ወይም የበዓላት ቀን ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚዘጋና የሚከፈት ሲሆን ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ ቢቀር የጨረታውን መከፈት አያስተጓጉልም።
  9.  በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለፀላቸው ከ7 የሥራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ዉል መፈረም እና ያሸነፉበትን ዋጋ ሙሉ በሙሉ መክፈል ይኖርባቸዋል፡፡ ሆኖም ሙሉ ከፍያውን በተጠቀሰው ጊዜ ገደብ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ተወርሶ ለመንግሥት ገቢ ይደረጋል።
  10. ቅ/ፅ/ቤቱ ያወጣውን የጨረታ ሰነድ በሥሙ ወይም በሕጋዊ ተወካዩ ሳይገዛ የተወዳደረ ማንኛውም ተጫራች ከተገኘ ከውድድር ውድቅ ይደረጋል።
  11. አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ገንዘብ አጠቃለው በከፈሉ በ10 ቀናት ውስጥ ንብረቶቹን የማንሳት ግዴታ ያለባቸዉ ሲሆን ይህ መሆን ካልቻለ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ተወርሶ ለመንግሥት ገቢ ይደረጋል፡፡ ዕቃውም በድጋሚ ለጨረታ ይቀርባል።
  12. ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ በስልክ ቁጥር 0915748790 ወይም 0913220473 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
  13. ቅ/ጽ/ቤቱ ጨረታውን መቀበል ወይም አለመቀበል የሚችል ሲሆን በማነኛውም ጊዜ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል ለመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻችን፡-ጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 05

ለተጨማሪ መረጃ ፡-በስልክ ቁጥር 0915748790 ወይም 0913220473

በጉምሩክ ኮሚሽን የጅግጅጋ ጉምሩክ ቅ/ፅ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-26
  • Publishing entity: Ethiopian Customs Commission
  • Bid bond: 10%
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 12, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders