የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን ያገለገሉ እቃዎች እና የማዕድን ተረፈ ምርቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል

Description

የሀገር ውስጥ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ቁጥር- EMC/OT/NCB/01/2018

የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን በዋናው መስሪያ ቤት ግቢ ውስጥ እና በቅርንጫፍ መስሪያ ቤት ያሉትን ያገለገሉ እቃዎችእና የማዕድን ተረፈ ምርቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።

ሎት

የዕቃው ዓይነት

ብዛት

የመጫረቻ ሰነድ የሚቀርብበትና  የሚዘጋበት የመጨረሻ

የመጫረቻ ሰነድ የሚከፈትበት

ቀን

ሰዓት

ቀን

ሰዓት

1

Iron ore

81.9 ton

18/09/2018

4:00

18/09/2018

4:30

2

Gelophany grease KAUS-45, Grat valve DN 400 (16 inch)

166 barrel

18/09/2018

4:00

18/09/2018

4:30

3

ፔሪዶት ( peridoite)

3267kg

18/09/2018

4:00

18/09/2018

4:30

በዚሁ መሰረት ተጫራቾች ለመወዳደር ሲመጡ ማሟላት የሚገባቸው ግዴታዎች፡-

  1. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የግዥ ዓይነት በዘርፉ ለ2018 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ (Value added tax) ተመዝጋቢ መሆናቸውን፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር(TIN)፣ እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችላቸው ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የሚሰጥ የታክስ ኪሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። እንዲሁም ለሎት 3 የማዕድን ማዘዋወርና ማስተላለፍ ፈቃድ ያለው መሆን አለበት።
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን በዚህ ማስታወቂያ በስተመጨረሻ በተገለጸው አድራሻ በቢሮ ቁጥር ብሎክ 2 በግንባር በመቅረብ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 300.00 / ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ሶፍት ኮፒ (soft copy) መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች ግዥ የሚፈጽሙበትን 2% (2 በመቶ) በኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖራሽን ስም( Ethiopian Mineral Corporation) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ብቻ ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታው አሸናፊዎች ከታወቀ በሶስተኛው ቀን በማስታወቂያ ቦርድ ይለጠፋል፡፡
  4. የጨረታ አሸናፊዎች ባስገቡት ዝርዝር መሰረት ገንዘቡን ከከፈሉበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀን ውስጥ ንብረቱን ማንሳት አለባቸው፡፡ የጭነት ማጓጓዟ የማቅረብ ሃላፊነት የገዥ ይሆናል። ሎት 1 ላይ ያለው IRON ORE 72 Tone የሚገኘው ቀንጢቻ ከ አ.አ 550 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው ፤ ሎት 2 ላይ የተጠቀሰውን በሚመለከት ማንኛውም ተጫራች ከመንግስት የማስወገጃ እውቅና የተሰጠው መሆኑን ወይም ቀጥተኛ ተጠቃሚ መሆናቸውን ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው በዚሁም መሰረት እቃውን ሲጭኑም ይዘው ሲያጓጉዙ ለሚከሰተው ማንኛውም ነግር ገዥ ሙሉ ሀላፊነቱን ይወስዳል፡፡ የሎት 2 ዕቃ የሚገኝበት ቦታ ቧንቧ ውሃ እና ሻኪሶ ከአዲሰ አበባ 500 ኪሎ ሜትር ላይ ነው፡፡
  5. ከጨረታ መዝጊያ ሰዓት በኋላ የሚቀርቡ የመጫረቻ ሠነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
  6. ተጫራቾች በመጫረቻ ሠነዳቸው ላይ ሶስት ማህተም ያረፈበት በማድረግ በፖስታው ጀርባ ላይ የድርጅታቸውን ስም፤የጨረታውን ሎትና ዓይነት ሙሉ አድራሻቸውን ጽፈው እና ፈርመው ማቅረብይኖርባቸዋል።
  7. ጨረታው የሚዘጋው እና የሚከፈተው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከላይ በሰንጠረዡ በተገለጸው ቀን መሰረት ሲሆን የመዝጊያ እና መክፈቻ ቀኑ በበዓል ቀን ከዋለ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን የሚከፈት ይሆናል።
  8. ተጫራቾች በሚሰጡት የዕቃ ዋጋ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስን (VAT)የማካተት ግዴታ አለባቸው ነገር ግን ተጫራቹ የተጨማሪ እሴት ታክስን ካላካተቱ ኮርፖሬሽኑ ተጫራቹ በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ቫትን ጨምሮ ይወሰዳል።
  9. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ፡- 22 ማዞሪያ አውራሪስ ሆቴል አጠገብ

በስልክ ቁጥር- 0911622263 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።

ኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን


Tender details

  • Deadline: 2026-05-26
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid opening: 2026-05-26 10:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopian Mineral Corporation (EMC)
  • Buyer address: 22 ማዞሪያ አውራሪስ ሆቴል አጠገብ
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 300.00 ብር በእያንዳንዱ ሎት
  • Published: May 12, 2026
  • Posted at: 2026-05-12T10:19:40.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders