የሰ/ሸዋ ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ተሽከርካሪዎችን መሸጥ ይፈልጋል
Description
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
በአፈ/ከሣሽ ፀደይ ባንክ (የቀድሞው አብቁተ አረርቲ ቅ/ጽ/ቤት) እና በአፈ/ተከሣሾች እነ በላቸው አንዱአለምና ጓደኞቻቸው የታክሲ አገልግሎት ህብረት ሽርክና ማህበር (11ሰዎች) መካከል ስለአለው የአፈፃፀም ክስ ክርክር ጉዳይ የአፈጻጸም ተከሣሽ ንብረት የሆኑት ባጃጆች፡-
1/ የሰሌዳ ቁጥሩ አማ 1-32672፣ የሞተር ቁጥሩAK4AJ44929570፣ የሻንሲ ቁጥር WAYACARWAJG006721፣
2/ የሰሌዳ ቁጥሩ አማ 1-32674፣ የሞተር ቁጥሩ AK4AJ4225905፣ የሻንሲ ቁጥር WAYACAHWAJG006625
3/ የሰሌዳ ቁጥሩ አማ 1-32675፣ የሞተር ቁጥሩ AK4A4429492 የሻንሲ ቁጥር WAYACARWAJG006715
የሆኑትን እያንዳንዳቸው በመነሻ ዋጋ በብር 263,461 /ሁለት መቶ ስልሳ ሶስት ሺህ አራት መቶ ስልሳ አንድ ብር/ በአረርቲ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ግቢ ተሽከርካሪዎቹ በቆሙበት ሰኔ 06 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በተራ ቁጥር 1ኛ እና 2ኛ የተጠቀሱት ባጃጆች ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት በተራ ቁጥር 3 የተጠቀሰው ባጃጅ ከ8፡00 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት በጨረታ እንዲሸጥ ፍ/ቤቱ አዟል።
በመሆኑም፡-
1. ተጫራቾች ያሸነፉበትን 1/4ኛውን በሲፒኦ ወዲያውኑ ለሀራጅ ባዩ የማስያዝ ግዴታ አለባቸው።
2. ተጫራቾች ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
3. ንብረቱን ለመሸጥ ምክንያት የሆነው ለፍርድ ማስፈፀሚያ ነው።
4. ገዥው በጨረታ ለገዛው ንብረት ዋጋውን ሣይከፍል የቀረ እንደሆነ ወይም በህግ በተወሰነው በዚሁ የሽያጭ ማስታወቂያ ላይ በተገለፀው መሠረት ዋጋውን ያላስቀመጠ እንደሆነ ሽያጩ ይሠረዛል፣ በፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ/429/2/ መሠረት ለሃራጅ ማስታወቂያው የተደረገውን ወጪ እንዲከፍል ይገደዳል።
5. የሐራጅ ማስታወቂያውን ለማቋረጥ የሚቻልበት የተሻለ መንገድ ካለ የጨረታ ማስታወቂያው በማንኛውም ጊዜ ሊቋረጥ ይችላል።
የሰ/ሸዋ ዞን ከፍ/ፍ/ቤት
ደ/ብርሃን
Tender details
- Deadline: 2026-06-13
- Bid closing time: 17:00
- Bid closing (note): የጨረታው መዝጊያ ቀን በየሎቱ የተለያየ ነው
- Bid opening: 2026-06-13 17:00
- Bid opening (note): የጨረታው መክፈቻ ቀን በየሎቱ የተለያየ ነው
- Region: Amhara
- Publishing entity: North Shewa Zone Higher Court
- Published: May 13, 2026
- Posted at: 2026-05-13T08:17:22.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.