በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ጽ/ቤት የተለያዩ 6 (ስድስት) አይነት የሰራተኞች ደንብ ልብስ ስፌት አገልግሎት ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር ሰሜ/አ/አ/ግ/ጨ/009/2018

የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን በሪጅኑ ስር ለሚገኙ የሥራ ክፍሎች እና በአገልግሎት መስጫ ማዕከላት ለሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የሚውል የተለያዩ 6 (ስድስት) አይነት የሰራተኞች ደንብ ልብስ ስፌት አገልግሎት ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች ላይ ለመግዛት ይፈልጋል።

የዕቃው አይነት

የመዝጊያ ቀን እና ሰዓት

የመክፈቻ ቀን እና ሰዓት

የጨረታ ዋስትና መስከበሪያ

የተለያዩ 6 (ስድስት) አይነት የሰራተኞች ደንብ ልብስ ስፌት አገልግሎት ግዥ

ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡00 ሰዓት

ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም 8፡30 ሰዓት

ብር 35,000.00 (ሰላሳ አምስት ሺህ)

 

  1. ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨ.እ.ታ፣ የግብር ከፋይ መ/ቁጥር እና ከገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ የሚል ማስረጃ ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል።
  2. ተጫራቾች የመንግስት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ድህረ-ገፅ ላይ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው።
  3. በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች በማያያዝ መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ዝርዝር ሁኔታው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ይገኛል።
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000149984384 (EEU N/A/A/R CU CON FOR EL CON) በሚለው ገቢ በማድረግ እና የከፈሉበትን የባንክ ስሊፕ ይዞ በመምጣት መውሰድ ይችላሉ።
  5. አድራሻ፡-ፒያሳ አቡነጴጥሮስ ፊት ለፊት አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር-210 በሚገኘው ሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ሰፕላይ ቼይን ግዥ እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ፣
  6. ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዡ ውስጥ በተገለፀው  መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ሲፒኦ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  7. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል በአንድ ላይ በማድረግ  «ኦሪጅናል እና ኮፒ» በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ እና ሁለቱን በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥር ሰሜ/አ/አ/ግ/ጨ/009/2018 የሚል ምልክት  በማድረግ እስከ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተራ ቁጥር 5 ላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ውስጥ ማስገባት የሚኖርባቸው ሲሆን ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
  8. ጨረታው ከላይ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
  9. ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 09 84 82 00 07 መደወል ይችላሉ።
  10. ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሰሜን አዲስ አበባ ሪጅን ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-29
  • Bid closing time: 14:00
  • Bid opening: 2026-05-29 14:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: Ethiopia Electrical Utility North Addis Ababa District
  • Bid bond: 35,000.00 ብር
  • Bid document price: 400.00 ብር
  • Published: May 17, 2026
  • Posted at: 2026-05-18T08:18:39.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders