የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ለሴፈቲኔት ፕሮግራም የሙያ የግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ አገልግሎት የሚውል ቡሎኬትና ሎካል ማቴርያል በሴፊቲኔት ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል
Description
ለ2ኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ጽህፈት ቤት ለሴፈቲኔት ፕሮግራም የሙያ የግንባታ ሥራ ማስፈፀሚያ አገልግሎት የሚውል ቡሎኬትና ሎካል ማቴርያል በሴፊቲኔት ከፀደቀ በጀት በሀገራዊ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ባለሙያዎች እንድትወዳደሩ ይጋብዛል።
- ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፣ የንግድ ምዝገባ መለያ ቁጥር/in No./፣ የዘመኑ የታደሰ የአቅቢነት ሰርተፍኬት /በኦንላየን በፌዴራል በአቅቢነት ዝርዝር የተመዘገበበት ማስረጃ/ ፣ የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ ጊዜው ያላለፈበት የቫት ዲክላሬሽን እና የኮንስትራክሽን የብቃት ማረጋገጫ ቅጂ ከዋናው ዶክመንት ጋር ማቅረብ የምትችሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ከግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ.ም 11:30 ሰዓት የማይመለስ በኢትዮጵያ ገንዘብ 400.00 /አራት መቶ ብር/ እየከፈላችሁ ከዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት በግዥ ቢሮ ቁጥር 7 የጨረታ ሰነድ መውሰድ ትችላላችሁ ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለቡሎኬት አቅራቢዎች በኢትዮጵያ ገንዘብ 20,000.00/ ሃያ ሺህ ብር ብቻ/ ፣ ሎካል ማቴሪያል አቅራቢዎች በኢትዮጵያ ገንዘብ 20,000.00/ሃያ ሺህ ብር ብቻ/ በባንክ የተረጋገጠ የባንክ ክሬዲት ሌተር፣ በሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ማስያዝ አለባችሁ።
- የጨረታው ሳጥን በዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ የሚገኝ ሲሆን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተጫራቾች ክፍት ይሆናል።
- ጨረታው ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ በተመሳሳይ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 በዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። የሚሞላው ዋጋ ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም ስርዝ ድልዝ ካጋጠመ የባለቤቱ ፊርማ መደረግ አለበት ።
- የሚሞላው ዋጋ ከነቫቱ መሆኑንና አለመሆኑን ሊገለፅ ይገባል፤ ካልተገለፀ ደግሞ የተሞላው ዋጋ ግዥ ፈፃሚ አካል ከነቫቱ መሆኑ ታሳቢ ያደርጋል።
- መስሪያ ቤታችን ይህን ጨረታ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ ማብራሪያ በስራ ሰዓት በአካል ወደ መስሪያ ቤታችን በመመጣት ወይም በሞባይል ቁጥር 0914123546 ወይም 0941336816 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል ።
የዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-06-05
- Publishing entity: ዓዲግራት ከተማ ዕቅድና ፋይናንስ ፅህፈት ቤት
- Bid bond: 20,000.00 ብር ለእያንዳንዱ
- Bid document price: 400.00 /አራት መቶ ብር/
- Published: May 20, 2026
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.