የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት የካራቆሬ ስቶር የሼድ ወለል/የመሬት ስራ፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ የሃርድ ኮር (ማሻሻታ) እና የኮንክሪት ወለል አገልግሎት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EEU/PPMNCB/15/2018
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት የካራቆሬ ስቶር የሼድ ወለል/የመሬት ስራ፣ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ የሃርድ ኮር (ማሻሻታ) እና የኮንክሪት ወለል አገልግሎት በዘርፉ ከተሰማሩ ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ድርጅቶች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡና በመስኩ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፣
- የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል የኢኤአ ፕሮጀክቶች ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት በማህበራዊ ዋስትና ህንፃ ከ11ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው በግዥ ፈጻሚው መ/ቤት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 175,000.00 (አንድ መቶ ሰባ አምስት ሺ ብር) በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የዋስትና ጊዜው ከሚያበቃበት ቀን በኃላ 28 ቀን ተጨማሪ ጊዜ ያለው የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) በኢኤአ ፕሮጀክት ፖርትፎልዮ ማኔጅመንት ወይም EEU-PPM ስም ተዘጋጅቶ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎኘ በማድረግ እና ጨረታ ቁጥር EEU/PPM NCB/15/2018 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 8:00 ሰዓት ድረስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት ዋስትና የንግድ ማዕከል ህንፃ 11ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው በግዥ ፈጻሚው መ/ቤት በመምጣት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- የጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ባይገኙም ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከ ቀኑ 8.30 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
- ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ የጨረታ ሰነዱን በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ጠዋት ከ2፡00-6፡00 ከ ሰዓት 7፡00 –11፡00 እና ቅዳሜ ጠዋት ከ 2፡00 – 6፡00 መመልከት ይቻላል።
- የፕሮግራም ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፍል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር፡- 011-1-26-31-53 መደወል ይችላሉ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት
Tender details
- Deadline: 2026-06-05
- Bid closing time: 14:00
- Bid opening: 2026-06-05 14:30
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የፕሮጀክቶች ፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት ጽ/ቤት
- Bid bond: 175,000.00 ብር
- Bid document price: 300.00 ብር
- Published: May 22, 2026
- Posted at: 2026-05-22T07:53:34.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.