ማስተር ቢዩልደር ሴንተር በጎ አድራጎት ድርጅት የኦዲት አገልግሎት ግዥ በውስን ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የኦዲት አገልግሎት ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር MBC/001/2018

ማስተር ቢዩልደር ሴንተር በጎ አድራጎት ድርጅት የኦዲት አገልግሎት ግዥ  በውስን ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

ስለዚህ ተጫራቾች ከታች የተዘረዘረ የምታሟሉ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

1. የጨረታው መስፈርቶች

የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ ዋና ምዝገባ፣ የታከስ ክሊራንስ ሰርተፍኬት፣ የሙያ ፈቃድ ከዚህ በፊት የሰሯቸው ስራዎች፣ የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ዋናውና ኮፒውን በመያዝ ጨረታውን መወዳደር ይችላሉ።

2. ተጫራቾች ለአገልግሎት የሚያስገቡትን ዋጋ እና የሚፈጅባቸውን ጊዜ አንደ ዋና (original) የጨረታ ሰነድ ለብቻው በሰም በታሸገ ፖስታ ታሽጎ እና ሁሌም ከላይ የተጠቀሱት ሰነድ ቅጂዎች በአንድ ላይ በትልቅ ፖስታ በኤንቨሎፕ በሰም የታሸገ መሆን አለበት።

3. ተጫራቾች የሚያቀርቡበት የጨረታ ሰነድ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም:: የተሰረዘ ሰነድ በፊርማ መረጋገጥ አለበት።

4. የጨረታ ሰነድ የማስገቢያ የመጨረሻ ቀን ግንቦት 18/2018 ዓም ከጠዋቱ 4:00 ድረስ ሲሆን በአካል መካኒሳ ሴሚናሪ ህንፃ በሚገኘው ቢሮ ቁጥር F2-026 በመምጣት ወይም በEmail MBC251222gmail.Com  ማስገባት ይችላሉ ።

5. ጨረታው የሚከፈተው በዚሁ ቀን ግንቦት 18/2008 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙባቸው ቢሮ ቁጥር F2 026 ይሆናል:: ከላይ የተገለፁትን መስፈርቶች ያላሟሉ ተጫራቾችን ወዲያውኑ ከጨረታ ውድድር ውጭ እንደሚሆኑ እንገልፃለን። ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911 059 878 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

ማስታወሻ፡- ድርጅቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ማስተር ቢዩልደር ሴንተር በጎ አድራጎት ድርጅት


Tender details

  • Deadline: 2026-05-26
  • Bid closing time: 10:00
  • Bid opening: 2026-05-26 10:30
  • Region: Addis Ababa
  • Publishing entity: ማስተር ቢዩልደር ሴንተር በጎ አድራጎት ድርጅት
  • Published: May 24, 2026
  • Posted at: 2026-05-25T08:11:02.000Z

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders