አዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አ.ማ. የተለያዩ ያገለገሉ ዕቃዎች ባሉበት ደረጃ በዝግ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል
Description
ያገለገሉ ንብረቶች ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር/001/2018
አዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አ.ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ያገለገሉ ዕቃዎች ባሉበት ደረጃ በዝግ ጨረታ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ሎት - 1 - የመጸዳጃ ቤት ዕቃዎች ሎት - 2 - አልሙኒየም ሎት - 3 - መስታወቶች ሎት - 4 - ብረቶችና ኤጋ ቆርቆሮ ሎት - 5 - ልዩ ልዩ መብራቶች ሎት - 6 - ሊፍቶች ሎት - 7 - የወለል ንጣፍ (SPC) |
ሎት - 8 - የእንጨት በሮች ሎት - 9 - መጋረጃ እና ምንጣፍ ሎት - 10 - ፈርኒቸር ሎት - 11 - የቢሮ ዕቃዎች ሎት - 12 - ባህላዊ ቤት ማስዋቢያ ሎት - 13 - ያገለገለ ተሽከርካሪ
|
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣ በኋላ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት ብር 500 (አምስት መቶ) በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አ.ማ ስም በተከፈተው አካውንት ቁጥር 1000616070839 ገቢ በማድረግ ያስገቡበትን ሰነድ በመያዝ ክጽ/ቤቱ ቢሮ ቁጥር 313 ተገኝተው ደረሰኝ መውሰድ ይችላሉ።
በዚህም መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የጨረታ ቅድመ-ሁኔታዎች እና መስፈርቶች ማሟላት የሚችሉ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ።
- ከጨረታው መዝጊያ ቀን እና ሰዓት በኋላ የሚቀርቡ የመወዳደሪያ ሰነዶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ተጫራች ለጨረታ ማስከበሪያ ከሚመረትበት ጠቅላላ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4) ወይም 25% በባንክ በተረጋገጠ በክፍያ ማዘዣ ሲፒኦ /CPO/ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ኢማ ስም አሰርተው በታሸገ ኢንቬሎፕ ከነሙሉ አድራሻው በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውንም ተጫራች የሚገዛውን የንብረት አይነት በመጥቀስ በኩባንያው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ ሞልቶ በታሸገ ኢንቨሎፕ (ፖስታ) በማድረግ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል።
- የጨረታው መወዳደሪያ ሰነድ ግልፅ እና ስርዝ ድልዝ የሌለው መሆን ይኖርበታል። ስርዝ ድልዝ የተደረገበት ዋጋ ከሆነ በመጫረቻ ሰነዱ ላይ ፈራሚ አካል ፓራፍ/ኢንሺያል ፊርማ ማድረግ ይኖርበታል::
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በአሃዝ እና በፊደል እንዲሁም ከቫት በፊት እና በኋላ መሆኑ መገለፅ አለባቸው።
- ተጫራቾች ንብረቶቹን ግንቦት 28 እና 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጠዋት ከ3፡00 6፡00 እና ከሰዓት ከቀኑ 7፡30 – 11፡00 በእያንዳንዱ ቀን ቀደም ብሎ ቀጠሮ በማስያዝ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 13 ሲ ኤም ሲ አደባባይ ፀሀይ ሪል እስቴት ፊት ለፊት በሚገነኘው የኩባንያው ንብረት ክፍል ውስጥ ማየት ይቻላሉ።
- የጨረታ መዝጊያ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እና መክፈቻ ቀን ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ይሆናል። ጨረታው በኩባንያው ንግድ ማዕከል ህንፃ 3ኛ ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን ያሸነፈበትን ሙሉ ክፍያ በመፈፀም ያስያዘውን ሲፒኦ (CPO) መውሰድ የሚችል ሲሆን ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሊፒኦ (CPO) አሸናፊው ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 3 (ሶስት) የስራ ቀናት ጊዜ ውስጥ ይመለስላቸዋል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ወይም በማስታወቂያ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በ3 የስራ ቀናት ውስጥ ገንዘቡን ለኩባንያው ከፍለው ንብረቱን በ3 ቀናት ውስጥ መረከብና በራሳቸው ወጪ ማንሳት ይኖርባቸዋል።
- በተባለው ጊዜ ክፍያውን ገቢ ያላደረጉም ሆነ ገቢ አድርገው ንብረቱን ተረክበው ያልወሰዱ ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ /ሲፒኦ/ ለኩባንያው ገቢ ሆኖ ንብረቱ እንደ አስፈላጊነቱ ለሁለተኛ አሸናፊ ወይም በድጋሚ ሰጨረታ ይቀርባል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ለተጫረቱበት ንብረት ተጨማሪ እሴት ታክስ ይከፍላሉ።
- ኩባንያው ስለንብረቶቹ አሻሻጥ የተሻለ መንገድ ካገኘ ሽያጩን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል ኢማ
አድራሻ፦ ለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 13 ሲ ኤም ሲ አደባባይ ፀሀይ ሪል እስቴት ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 011 667 0082
Tender details
- Deadline: 2026-06-12
- Bid closing time: 14:00
- Bid opening: 2026-06-12 14:30
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: አዲስ ዓለምአቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል አማ
- Bid bond: 25%
- Bid document price: 500.00 ብር
- Published: May 24, 2026
- Posted at: 2026-05-25T09:17:14.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.