ስማርት ዲጂታል ቴክኖሎጂስ አ.ማ. ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት የድርጅቱን ሂሳብ በተመሰከረለት የውጪ ኦዲተር ማስመርመር ይፈልጋል
Description
የኦዲት ስራ የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ስማርት ዲጂታል ቴክኖሎጂስ አ.ማ በ ኢትዮ ቴሌኮም በሃገር አቀፍ ደረጃ የቴሌኮም ምርቶችን በማከፋፈል እየሰራ የሚገኝ ድርጅት ነው።
በዚህም መሰረት ድርጅታችን ለሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት የድርጅታችን ሂሳብ በተመሰከረለት የውጪ ኦዲተር ማስመርመር ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት፡-
በዋናው ኦዲተር የተመዘገበ ሆኖ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የታክስ መለያ ቁጥርና የሙያ ማረጋገጫ ያለው/ያላት
የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው መረጃ ማቅረብ የሚችል/የምትችል
ከፌዴራል ወይም ክልል ኦዲት መስሪያ ቤት ለበጀት ዓመቱ የታደሰ ፍቃድ ያለው/ያላት
በመሆኑም ሂሳቡን ለመመርመር የሚጠይቀውን የገንዘብ መጠን(ቫትን ጨምሮ) እና ስራውን ለማጠናቀቅ የሚፈጀውን ጊዜ በመጥቀስ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀመሮ ባሉት 7 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የተጠየቁትን ማስረጃዎች የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በማያያዝ ከታች በተጠቀሰው አድራሻ በስራ ሰዓት ገቢ በማድረግ ማመልከት የሚቻል መሆኑን እናሳውቃለን።
ድርጅቱ ሌላ አማራጭ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
አድራሻ ቦሌ ኦሮሚያ ህንፃ 2ኛ ፎቅ (ቢሮ ቁጥር 205)
ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት በስልክ ቁጥር፡- 0924156865 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
ስማርት ዲጂታል ቴክኖሎጂስ አ.ማ
Tender details
- Deadline: 2026-06-06
- Publishing entity: Smart Digital Technologies S.C
- Published: May 31, 2026
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.