በደቡብ ኢትዮጵያ ክ/መ/ጤና ቢሮ በጎፋ ዞን ጤና መምሪያ ሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የደንብ ልብስ ለአስተዳደር ሠራተኞች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል

Description

የጨረታ ማስታወቂያ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክ/መ/ጤና ቢሮ በጎፋ ዞን ጤና መምሪያ ሣውላ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የደንብ ልብስ ለአስተዳደር ሠራተኞች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

በዚህ መሠረት ፡-

ከዚህ በታች የሚከተሉትን መስፌርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን።

  1. በዘርፉ የተሰማራ የንግድ ፍቃድ ያለው/ያላት
  2. የ2018 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችል /የሚትችል
  3. የንግድ ምዝገባ ምስክር ወርቀት ማቅረብ የሚችል /የሚትችል
  4. የቫት ተመዝጋቢ የሆነች
  5. የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር /TN No/ ያለው/ያላት
  6. የ2017 ዓ/ም ግብር ከፍሎ ያጠናቀቀች
  7. የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል/የሚትችል
  8. የ2017 በጀት ዓመት መልካም የአፈፃፀም ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል የሚትችል
  9. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚወዳደሩበትን የሽያጭ ጠቅላላ ዋጋ 2% በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO) ማቅረብ አለባቸው።
  10. የጨረታ ሰነድ መግዣ ብር 200 (ሁለት መቶ) ብር ብቻ ጨረታው ከወጣበት ቀን እስከ 15 ኛው ቀን 11፡30 ድረስ ባሉት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቢሮ ቁጥር-7 በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
  11. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው ቀን በ3፡00 ሰዓት ታሽጎ 3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበት ስሆን ባይገኙ ጨረታዉን መክፈት አያዳግትም።
  12.  የጨረታ አሸናፊዉ የአስተዳደር ሠራተኛው ደንብ ልብስ ጨርቅ ናሙና ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ በናሙናዉ መ/ቤቱ ካልተስማማ መ/ቤቱ ራሱ በሚያቀርበዉ ናሙና መሠረት ይሆናል።
  13. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፌውን ደንብ ልብስ እስከ ተቋሙ ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርበታል።
  14. መ/ቤቱ የተሸለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  15. ተጫራቾች ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 7 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0913686457 / 092534768 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።

ማሳሰቢያ ፡- የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን እሁድና ቅዳሜ ወይም ህዝባዊ በዓል ባለበት ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክ/መ/ጤና ቢሮ በጎፋ ዞን ጤና መምሪያ ሣውላ

አጠቃላይ ሆስፒታል


Tender details

  • Deadline: 2026-06-15
  • Publishing entity: Sawula General Hospital
  • Bid bond: 2%
  • Bid document price: 200.00 ብር
  • Published: May 30, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders