በጋሞ ዞን የካምባ ዙርያ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት የተለያዩ ብረታ ብረቶች፣ የመኪና ጎማዎች፣ ሞተሮች፣ የመኪና ዉዳቂ ክፍሎች አሮጌ የኮምፕዩተር ስፔርፓርቶች፣ የተገነጣጠሉ ጋሪዎች እና ሌሎች የሚወገዱን ብረቶች በቆራሊዮ መልክ በኪሎ በግልጽ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

በጋሞ ዞን የካምባ ዙ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት በ2018 ዓ/ም በጀት ዓመት አገልግሎት መስጠት የማይችሉ የተለያዩ ብረታ ብረቶች፤ የመኪና ጎማዎች፤ ሞተሮች፤ የመኪና ዉዳቂ ክፍሎች አሮጌ የኮምፕዩተር ስፔርፓርቶች፤ የተገነጣጠሉ ጋሪዎች እና ሌሎች የሚወገዱን ብረቶች በቆራሊዮ መልክ በኪሎ በግልጽ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።

በዚህ መሠረት፡-

  • ተጫራቾች ዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸዉ መሆን ይጠበቅባቸዋል ፤
  • ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ለ15 ቀናት ይቆያል
  • የጨረታው ሰነድ ካምባ ዙ/ወ/ገ/ባ/ቅ/ጽ/ቤት 600.00 / ስድስት መቶ ብር / ገቢ በማድረግ መውሰድ ይችላሉ
  • ተጫቾች የጨረታ ማስከበረያ 18,000.00 / አስራ ስምንት ሺህ ብር / በባንክ የተረጋገጠ CPO ማስያዝ የሚችሉ መሆን አለባቸው ፤
  • የጨረታ ሰነድ የሚሸጥበት ጊዜ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 15 ቀናት ከ3፡00 – 11፡00 ሰዓት ድረስ ይሆናል
  • የጨረታ ሰነዱን (አንድ) ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታ ሞልተው በ16ኛው የሥራ ቀን 4፡00 ሰዓት በጨረታ ሳጥን ውስጥ ገብተው ይታሸጋል
  • ጨረታው የሚከፈተው በካምባ ዙ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ16ኛው የሥራ ቀን በ4፡30 ሰዓት ይሆናል። 16ኛው ቀን የሥራ ካልሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
  • ተጫራቾች ዋጋ ከመሙላታቸዉ በፊት ንብረቶችን ካምባ ዙ/ወ/ፋ/ጽ/ቤት ቀርቦ ማየት ይችላሉ
  • አሽናፊው የሚለየው ባቀረበዉ በነጠላ ዋጋ ሲሆን ሻጭ መ/ቤቱ ብረቱን በኪሎ ለክቶ የሚሸጥ ይሆናል
  • መጫረት የሚፈልጉ የጨረታ መነሻ ዋጋ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነዱ ላይ ይገኛል
  • ከተሸጡ ንብረቶች የሚፈለግ ቀረጥ / ታክስ/ ካለ በገዥ የሚሸፍን ሲሆን ይሆናል
  • የጨረታ አሸናፊ የገዛውን ንብረቶች ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የገዛበትን ገንዘብ ሙሉ በሙሉ ገቢ በማድረግ ንብረቶችን የሚረከብ ሲሆን ይህ ካልሆነ ጨረታው ተሰርዞ ለማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለመንግስት ገቢ ይሆናል
  • መ/ቤቱ ለንብረቱ ሸያጭ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል መሰረዝ ይችላል።

ለበለጠ መረጃ፡- 09-16-10-42-78 ወይም 09-64-94-78-25 ይደዉሉ።
በጋሞ ዞን የካምባ ዙርያ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት


Tender details

  • Deadline: 2026-06-08
  • Publishing entity: Kamba Zuriya Woreda Finance Office
  • Bid bond: 18,000(አስራ ስምንት ሺህ ብር)
  • Bid document price: 600.00 /ስድስት መቶ ብር/
  • Published: May 23, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders