የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ያገለገለ ተሽከርካሪ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ለአገልግሎት ሲጠቀምበት የነበረውን ያገለገለ ተሽከርካሪ ባለበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
1. የተሽከርካሪው ዝርዝር መረጃ
- የተሽከርካሪው ዓይነት (ሞዴል): ጃፓን ኒሳን ፓትሮል (Japan Nissan Patrol)
- የተመረተበት ዘመን፦ 2008 እ.ኤ.አ
- የነዳጅ ዓይነት፦ ናፍጣ (Diesel)
- አሁን ያለው የኪሎሜትር ንባብ፤- 155,000 ኪሜ
2. ለመወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች ማሟላት የሚገባቸው ቅድመ-ሁኔታዎች
ተጫራቾች የተሽከርካሪውን ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከአሶሴሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት መውሰድ ይችላሉ። ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ማረጋገጫ የሚሆን ባስገቡት ጠቅላላ የጨረታ ዋጋ ላይ አስር በመቶ (10% ) በባንክ የተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (CPO) በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸው። ማንኛውም ተጫራች የሚሰጠውን የዋጋ ማቅረቢያ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ አሶሴሽኑ ለዚህ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርበታል። ተጫራቹ አሽናፊ መሆኑ ከተገለጥጸበት ቀን ጀምሮ የተሽከርካሪውን ሙሉ ዋጋ በ5 ቀናት ውስጥ ክፍሎ በ15 ቀን ውስጥ ተሽከርካሪውን የማንሳት ግዴታ አለበት።
3. የተሽከርካሪው እይታ እና የጨረታው ማጠቃለያ
ማሳሰቢያ፦ ተጫራቾች ተሽከርካሪውን አሶሴሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ በሥራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ ዓርብ) በመገኘት መመልከት ይችላሉ።
- የጨረታ ማስገቢያ የመጨረሻ ቀን፦ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት።
- የጨረታ ሳጥን መክፈቻ፦ ጨረታው በሚዘጋበት ዕለት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአሶሴሽኑ የስብሰባ አዳራሽ ውስጥ ከጠዋቱ 4:15 ላይ ይከፈታል።
4. አድራሻ
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ አሶሴሽን ዋና መሥሪያ ቤት ፦ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 13 (ከሲኤምሲ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አጠገብ)
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር +251-11-6-45-32-00
(አሶሴሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡)
Tender details
- Deadline: 2026-07-06
- Bid closing time: 10:00
- Bid opening: 2026-07-06 10:15
- Region: Addis Ababa
- Publishing entity: Ethiopia Economics Association
- Bid bond: 10%
- Bid document price: 300.00 (ሶስት መቶ ብር)
- Published: Jun 21, 2026
- Posted at: 2026-06-22T12:39:33.000Z
Documents
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.