የቴሌ ጡረተኞች ማህበር ከሐምሌ 1 ቀን 2017 እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ሂሳብ ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል

Description

የኦዲት ሥራ ማስታወቂያ

የቴሌ ጡረተኞች ማህበር መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ሲሆን የማህበሩንና በሥሩ የሚያስተዳድረውን የጡረተኞች መዝናኛ ክበብ የ2018 (ከሐምሌ 1 ቀን 2017 እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም) በጀት ዓመት ሂሳብ ኦዲት ማስደረግ ይፈልጋል።

ከዚህ በታች የተዘረዘሩ መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች መወዳደር የምትችሉ መሆናችሁን እንገልጻለን።

1. የታደሰ የንግድ ፈቃድና የዘመኑ ግብር የተከፈለበት ማስረጃ፣

2. የሙያ ብቃት ሕጋዊነት በመንግስት የታወቀና የተመዘገበ፣

3. የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚችል፣

4. የታክስ መለያ ቁጥር Tin Number ያላችሁ

ተወዳዳሪዎች የምትጠይቁትን የገንዘብ መጠንና ሥራውን አጠናቆ ለማቅረብ የሚወስደውን ጊዜ በመጥቀስ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሰባት(7) ተከታታይ የሥራ ቀናት ዋናውንና ኮፒ ማስረጃዎቻችሁን በመያዝ በሥራ ሰዓት ፒያሳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም ግቢ የቴሌ ጡረተኞች ማህበር ቢሮ ቁ. 39 በአካል ቀርባችሁ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁ. 0911225911 ወይም 0911211362
መደወል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻስን።
የቴሌ ጡረተኞች የመዝናኛና የመገናኛ ማህበር


Tender details

  • Deadline: 2026-07-22
  • Publishing entity: Tele Employees Retired Association
  • Published: Jul 15, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders