ሲንቄ ባንክ አ.ማ. መኪና በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል

Description

የሐራጅ ሽያጭ ማስታወቂያ
ቁጥር ሲባ/ህአዲ/ሐራጅ/035/2018

ሲንቄ ባንክ አ.ማ. በአዋጅ ቁጥር 1147/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ቀጥሎ የቀረበዉ ንብረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

የተበዳሪ ስም

የንብረት አስያዥ ስም

አበዳሪ ቅርንጫፍ

ለጨረታ የቀረበው ንብረት መግለጫ

የጨረታ መነሻ ዋጋ በብር

 

ጨረታው የሚከናወንበት

ጨረታው የወጣው

 

 

 

ቀን

ሰዓት

 

1

 

ጌትነት መገርሳ ጪብሳ

ጌትነት መገርሳ ጪብሳ

ኦዳ

ሱዙኪ እስዊፍት ሞዴል 2022

AA-02-C29379

MBHCZC63S00B41169

  1,824,000

24/11/2018

430-530

ለመጀመሪያ    ጊዜ

የሐራጁ ደንቦች፤  

  1. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪል የጨረታውን መነሻ ዋጋ አንድ አራተኛ (1/4ኛ) በባንክ ክፍያ ማዘዣ (ሲ.ፒ.ኦ.) ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ/ አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በአሥራ አምስት (15) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካል ከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ሐራጁ ይሰረዛል። በተጨማሪም ንብረቱ ድጋሚ ለሐራጅ ሲቀርብ ለሚታየው የዋጋ ልዩነት ይጠየቃል።                    
  2. በሐራጁ ሂዳት ከፍተኛ ዋጋ ያቀረበው ተጫራች ማን እንደሆነ ብቻ የሚገለፅ ሲሆን ጨረታውን ያሸነፈው ሰው/አካል ስለማሸነፉ በሚመለከተው የባንኩ አካል ከተረጋገጠ በኃላ ማሸነፉን የሚገልጽ ደብዳቤ ይሰጠዋል።
  3. ላላሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲ.ፒ.ኦ በዕለቱ ይመለስላቸዋል።
  4. በሐራጅ ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች፣ ተበዳሪ እና ንብረት አስያዥ ወይም ሕጋዊ ተወካዮች ብቻ ናቸው።
  5. ሐራጁ የሚካሄድበት ቦታ፤ ካዛንቺስ የምገኘዉ ሲንቄ ባንክ ዋና መስሪያ ቤት 7ኛ ፎቅ ይሆናል።
  6. በጨረታዉ ቀን ከ4፡30 እስከ 5፡00 የተጨራቾች ምዝገባ ሰዓት ሲሆን፣ ከ5፡00 ሰዓት በኋላ የተጫራች ምዝገባ አይኖርም። ከ5፡00 – 5፡30 ሐራጁ የሚካሄድበት ጊዜ ይሆናል።
  7. ለስም ዝውውር የሚከፈል ክፍያ እንዲሁም የሊዝ እና ሌሎች ገዥ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ከታክስ እና ግብር ጋር ተያያዥ የሆኑ ክፍያዎችን ገዢው/አሸናፊው ይከፍላል።
  8. የንግድ ማህበራትን በመወከል መጫረት የሚፈልግ ማንኛዉም ግለሰብ የማህበሩን ህጋዊ ሰዉነት ያለዉ መሆኑን የሚያረጋግጥ የመመስረቻ ወይም እና የመተዳደሪያ ደንብ እንዲሁም ህጋዊ የዉክልና ስልጣን ሰነድ ይዞ መቅረብ ይጠበቅበታል።
  9. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  10. ለሐራጅ የቀረበ ንብረትን ለመጎብኘት የሚፈልግ ከአበዳሪ ቅርንጫፍ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጎብኘት ይቻላል።
  11. ተጫራች የጨረታ አሸናፊ ነዉ የሚባለዉ አሸናፊነቱን የሚገልፅ  ደብዳቤ በፅሑፍ ሲደርሰዉ ነዉ።
  12. ለተጨማሪ መረጃ የሲንቄ ባንክ ህግ አገልግሎት ክፍል ስልክ ቁጥር (+251-11 557-6016), ፤ ኦዳ ቅርንጫፍ (011 557 1965) ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

ሲንቄ ባንክ አ.ማ.            


Tender details

  • Deadline: 2026-07-31
  • Publishing entity: Siinqee Bank Share Company
  • Bid bond: 25%
  • Published: Jul 15, 2026

Categories

Source

2merkato

Always verify against the original notice before bidding.

View original ↗
← Back to all tenders