በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የተለያዩ ማሽነሪዎች መለዋወጫ እቃዎች ግዥ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል
Description
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር EEP/EC/FP/NCB/01/2019
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የተለያዩ ማሽነሪዎች መለዋወጫ እቃዎች ግዥ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ በግዥ ኤጀንሲ የአቅራቢዎች ዝርዝር ድረ-ገጽ ላይ የተመዘገቡ መሆን አለባቸው
- ተጫራቾች ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በሥራ ቀንና ሰዓት የካ ክ/ከ ወረዳ 9 ኮተቤ ብረታ ብረት ፋብሪካ ፊት ለፊት በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መ/ቤት፣ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ፋይናንስ እና ግዥ ቢሮ የማይመለስ ብር 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/በመከፈል ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተገለጹትን ዕቃዎች በሚመለከት የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ዝርዝር በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ቁጥር EEP/EC/FP/NCB/01/2019 የሚል ምልክት በማድረግ በጨረታ ሰነዱ በተገለጸው መሠረት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
|
የአቅርቦት ግዥ ዓይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የጨረታው መዝጊያ ቀንና ሰዓት |
የጨረታው መክፈቻ ቀንና ስዓት |
|
የተለያዩ ማሽነሪዎች መለዋወጫ እቃዎች ግዥ |
ብር 400,000.00 |
ሀምሌ 22 ቀን |
ሀምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡15 ሰዓት |
- ገዥው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር +251 11 673 2198 መደወል ይችላሉ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ
ፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ
Tender details
- Deadline: 2026-07-29
- Publishing entity: Ethiopian Electric Power Engineering and Construction Business Sector Finance and Procurement Department
- Bid bond: 400,000.00 ብር
- Bid document price: 1000.00 ብር
- Published: Jul 20, 2026
- Posted at: 2026-07-21T07:42:58+00:00
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.