የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት የተለያዩ ኤሌክትሪክ ዕቃዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል
Description
ለሦስተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
- የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ በሚገኘው የአሶሳ ቅ/ጽ/ቤት ካምፓስ አካባቢ ባለው ቅጥር ግቢ እና መጋዘን የሚገኙትን የተለያዩ ኤሌክትሪክ ዕቃዎች እና ሌሎችም ዕቃዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ ተጫራቾች የተዘጋጀውን የሽያጭ ጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200/ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የአሶሳ ቅ/ጽ/ቤት በሚገኘው የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት መ/ቤት ቅጥር ግቢ ቢሮ ቁጥር 7 በመገኘት እና ክፍያ በመፈጸም ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ከሀምሌ 15/2018 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 27/2018 ዓ.ም ከቀኑ 6:30 ድረስ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይቻላል።
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚያቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% ለስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት/Refugees and Returnees Service /በሚል የተዘጋጀ የክፍያ ማዘዣ /CPO/ የባንክ ዋስትና /Bank Gurantee/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራች ከሀምሌ 15 እስከ ሀምሌ 27/ 2018 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት አሶሳ በሚገኘው የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ በመገኘት ዕቃዎቹን መመልከት ይችላል።
- ጨረታው አሶሳ በሚገኘው የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ የሚካሄድ ሲሆን የጨረታው ሳጥን ሀምሌ 27 ከቀኑ 7፡30 ታሽጎ በዕለቱ ከቀኑ 8፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊ ተጫራቾች ለጨረታው ያስያዙት ሲፒኦ ከሚከፍሉት ዋጋ ጋር የሚታሰብላቸው ሲሆን ለተሸናፊ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ዋስትና በ3 ቀናት ውስጥ ተመላሽ ይደረግላቸዋል።
- ተጫራቾች ማሸነፋቸው በደብዳቤ ወይም በማስታወቂያ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ5 ቀናት ውስጥ ያሸነፉትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃዎችን መረከብ አለባቸው።
- በተራ ቁጥር 6 በተገለጹት ቀናት ውስጥ ክፍያውን ገቢ ያላደረገ ተጫራች ለጨረታው ማስከበርያ ያስያዘው ሲፒኦ ለአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ገቢ በማድረግ የተሻለውን አማራጭ የመውሰድ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር +251952823095 ወይም 0577752465 ደውሎ መጠየቅ ይችላል።
አድራሻ፦ አሶሳ ከተማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አካባቢ ውሃና ፍሳሽ ጽ/ቤት ጎን
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
Tender details
- Deadline: 2026-08-03
- Publishing entity: Refugee and Returnee Service
- Bid bond: 2%
- Bid document price: 200.00 ብር
- Published: Jul 22, 2026
- Posted at: 2026-07-22T09:43:24.000Z
Categories
Source
2merkato
Always verify against the original notice before bidding.